ቀጥታ፡
አርእስተ ዜና
የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና በዘላቂነት የሚያረጋግጥ ነው - ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)
Oct 18, 2025 10
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት አርሶ አደሩ ዓመቱን በሙሉ በማምረት የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥና የገቢ አቅሙ እንዲጨምር የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ የሚገኘውን የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት ዛሬ መርቀዋል። የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) በምርቃቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ለዓመታት ሲባክን የነበረው የወልመል ወንዝ ዛሬ ተመርቆ የአካባቢውን ማህበረሰብ በልማት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የመስኖ ፕሮጀክቱ 20ሺህ የሚሆኑ አባውራዎችን ተደራሽ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።   አራት ዓመታትን የፈጀው የፕሮጀክቱ ግንባታ ስድስት ቢሊዮን ብር ወጪ እንደተረገበትም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው ላደረጉት ያልተገደበ ድጋፍና ላሳዩት በሳል አመራርም ሚኒስትሩ አመስግነዋል። አጠቃላይ ፕሮጀክቱ የውሃ መቀልበሻ ውቅር 33 ኪሎ ሜትር ውሃ ማስቀየሻ የመጀመሪያ ቦይ(ፕራይመሪ ካናል)፣ 47 ኪሎ ሜትር ሁለተኛ ቦይ(ሰከንደሪ ካናል) እና 64 ኪሎ ሜትር ሶስተኛ ቦይ(ቴርሸሪ ካናል) በድምሩ 144 ኪሎ ሜትር የቦይና 30 የውሃ ማጠራቀሚያዎች(ፖንዶችን) ያካተተ መሆኑንም ገልጸዋል። በተጨማሪም 60 ኪሎ ሜትር መጋቢ የመንገድ ስራዎች፣ 50 ብሎኮች የያዘ የግድብ አስተዳደርና ለማህበረሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶች የሚሰጥ ማዕከል ያለው መሆኑንም አብራርተዋል። የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ አርሶ አደሮች ዓመቱን ሙሉ እንዲያመርቱ፣ የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ፣ ለብዙ ዜጎች የስራ ዕድል እንዲፈጠር እንዲሁም የቆላማ አካባቢና የአርብቶ አደር ልማትን እውን እንደሚያደርግ ነው ሚኒስትሩ የገለጹት። በዘላቂነትም የአካባቢው ማህበረሰብ ምርትን በመጨመር የገቢ አቅሙን እንዲያሳድግ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።
የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን የማዘመን ስራ ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ጥረት ወሳኝ ነው
Oct 18, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን ለማዘመን እየተከናወነ ያለውን ተግባር ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት የጋራ ጥረት አስፈላጊ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ሰባተኛውን ሀገር አቀፍ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ዓመታዊ ጉባዔ አካሂዷል።   የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚህ ወቅት እንዳሉት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓትን ለማጠናከር የህግና አሰራር ስርዓቱን የማሻሻል ስራ ተሰርቷል። ከ4 ሺህ በላይ ተቋማት ውል በተገባለት የመድኃኒት ግዢ ውል መፈፀማቸውን አንስተው በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋናውን ጨምሮ 20 ማዕከሎች በዚሁ መሰረት ስራቸውን እያከናወኑ ነው ብለዋል። ይህንን ስራ እስከ ጤና ተቋማት ድረስ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው የመድኃኒት አቅርቦትን ማዘመን የጋራ ጥረትን የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዓለም ጤና ድርጅት ማቹሪቲ ሌቭል 3 መድረሷ ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም መሆኑን አንስተው ወደ ቀጣይ ደረጃ ለማድረስ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ያስፈልጋል ብለዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ በበኩላቸው የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ማምጣት ማስቻሉን አስረድተዋል። ከተቋማት ጋር ውል የተገባለት አቅርቦት ስርዓት በመፈራረም ወደ ስራ መግባቱን አውስተው በ2017 በጀት ዓመት 68 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የመድኃኒትና ሕክምና ግብዓት መሰራጨቱን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ እንደገለጹት፤ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማዘመንና የሀገር ወስጥ አምራቾችን ለማበረታታት የሚያስችል ስራ ተከናውኗል። በዚህም የሀገር ውስጥ አምራቾች ድርሻ 41 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፤ ፈጣንና ተጠያቂነት ያለው ስርዓት ለማጠናከር እንደሚሰራ ተናግረዋል። አገልግሎቱ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል። በጉባኤው የተሳተፉ አካላት የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻል የተከናወኑት ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አብዱልሙኒየም አልበሽር አገልግሎቱ ውል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት አበረታች ውጤት እየተመዘገበበትና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ይሄይስ ስብሃት በበኩላቸው ያገኙት የእውቅና ሽልማት ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ሶስት ዓመታት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን የሚያዘምኑ ስራዎች መከናወናቸው ለዘርፉ መነቃቃት አስተዋፅኦ ማበርከቱን የተናገሩት ደግሞ የክሊቺ ኢስትሮ ባዮቴክ መድኃኒት ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ዳንኤል ዋቅቶሌ ናቸው። በመድረኩ በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ስርዓት የተሻለ ስኬት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጥቷል።  
የሚታይ
የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና በዘላቂነት የሚያረጋግጥ ነው - ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)
Oct 18, 2025 10
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት አርሶ አደሩ ዓመቱን በሙሉ በማምረት የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥና የገቢ አቅሙ እንዲጨምር የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ የሚገኘውን የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት ዛሬ መርቀዋል። የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) በምርቃቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ለዓመታት ሲባክን የነበረው የወልመል ወንዝ ዛሬ ተመርቆ የአካባቢውን ማህበረሰብ በልማት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የመስኖ ፕሮጀክቱ 20ሺህ የሚሆኑ አባውራዎችን ተደራሽ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።   አራት ዓመታትን የፈጀው የፕሮጀክቱ ግንባታ ስድስት ቢሊዮን ብር ወጪ እንደተረገበትም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው ላደረጉት ያልተገደበ ድጋፍና ላሳዩት በሳል አመራርም ሚኒስትሩ አመስግነዋል። አጠቃላይ ፕሮጀክቱ የውሃ መቀልበሻ ውቅር 33 ኪሎ ሜትር ውሃ ማስቀየሻ የመጀመሪያ ቦይ(ፕራይመሪ ካናል)፣ 47 ኪሎ ሜትር ሁለተኛ ቦይ(ሰከንደሪ ካናል) እና 64 ኪሎ ሜትር ሶስተኛ ቦይ(ቴርሸሪ ካናል) በድምሩ 144 ኪሎ ሜትር የቦይና 30 የውሃ ማጠራቀሚያዎች(ፖንዶችን) ያካተተ መሆኑንም ገልጸዋል። በተጨማሪም 60 ኪሎ ሜትር መጋቢ የመንገድ ስራዎች፣ 50 ብሎኮች የያዘ የግድብ አስተዳደርና ለማህበረሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶች የሚሰጥ ማዕከል ያለው መሆኑንም አብራርተዋል። የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ አርሶ አደሮች ዓመቱን ሙሉ እንዲያመርቱ፣ የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ፣ ለብዙ ዜጎች የስራ ዕድል እንዲፈጠር እንዲሁም የቆላማ አካባቢና የአርብቶ አደር ልማትን እውን እንደሚያደርግ ነው ሚኒስትሩ የገለጹት። በዘላቂነትም የአካባቢው ማህበረሰብ ምርትን በመጨመር የገቢ አቅሙን እንዲያሳድግ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።
የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን የማዘመን ስራ ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ጥረት ወሳኝ ነው
Oct 18, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን ለማዘመን እየተከናወነ ያለውን ተግባር ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት የጋራ ጥረት አስፈላጊ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ሰባተኛውን ሀገር አቀፍ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ዓመታዊ ጉባዔ አካሂዷል።   የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚህ ወቅት እንዳሉት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓትን ለማጠናከር የህግና አሰራር ስርዓቱን የማሻሻል ስራ ተሰርቷል። ከ4 ሺህ በላይ ተቋማት ውል በተገባለት የመድኃኒት ግዢ ውል መፈፀማቸውን አንስተው በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋናውን ጨምሮ 20 ማዕከሎች በዚሁ መሰረት ስራቸውን እያከናወኑ ነው ብለዋል። ይህንን ስራ እስከ ጤና ተቋማት ድረስ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው የመድኃኒት አቅርቦትን ማዘመን የጋራ ጥረትን የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዓለም ጤና ድርጅት ማቹሪቲ ሌቭል 3 መድረሷ ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም መሆኑን አንስተው ወደ ቀጣይ ደረጃ ለማድረስ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ያስፈልጋል ብለዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ በበኩላቸው የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ማምጣት ማስቻሉን አስረድተዋል። ከተቋማት ጋር ውል የተገባለት አቅርቦት ስርዓት በመፈራረም ወደ ስራ መግባቱን አውስተው በ2017 በጀት ዓመት 68 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የመድኃኒትና ሕክምና ግብዓት መሰራጨቱን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ እንደገለጹት፤ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማዘመንና የሀገር ወስጥ አምራቾችን ለማበረታታት የሚያስችል ስራ ተከናውኗል። በዚህም የሀገር ውስጥ አምራቾች ድርሻ 41 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፤ ፈጣንና ተጠያቂነት ያለው ስርዓት ለማጠናከር እንደሚሰራ ተናግረዋል። አገልግሎቱ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል። በጉባኤው የተሳተፉ አካላት የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻል የተከናወኑት ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አብዱልሙኒየም አልበሽር አገልግሎቱ ውል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት አበረታች ውጤት እየተመዘገበበትና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ይሄይስ ስብሃት በበኩላቸው ያገኙት የእውቅና ሽልማት ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ሶስት ዓመታት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን የሚያዘምኑ ስራዎች መከናወናቸው ለዘርፉ መነቃቃት አስተዋፅኦ ማበርከቱን የተናገሩት ደግሞ የክሊቺ ኢስትሮ ባዮቴክ መድኃኒት ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ዳንኤል ዋቅቶሌ ናቸው። በመድረኩ በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ስርዓት የተሻለ ስኬት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጥቷል።  
የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት እንደሚያጠናክር ገለጸ
Oct 18, 2025 49
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ ለዘላቂ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ አረጋገጠ። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት አጃይ ቡሻን ፓንዲ ጋር የሁለትዮሽ ትብብሮች ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በዚሁ ወቅት አቶ አሕመድ እንዳሉት፥ የታዳጊ ሀገራትን የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ለማሳደግ ብሎም ከአየር ንብረት ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስ በፋይናንስ አቅርቦት ላይ በትብብር መሥራት ይገባል። ባንኩ ባለፉት ዓመታት ወሳኝ የሆኑ የመሠረተ ልማት ፍላጎቶችን ለመደገፍ ያደረገውን ጥረትም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ ስለምትገነባው ግዙፉ አዲሱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክትም ገለጻ አድርገዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በኢነርጂ ዘርፍ ለሚሠሩ ዋና ዋና ፕሮጀክቶች የባንኩ ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል። አጃይ ቡሻን ፓንዲ በበኩላቸው፤ኢትዮጵያ እያካሄደች ላለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና መንግሥት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ የሰጠውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከር እና ሀገሪቱ ለዘላቂ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ባንኩ ቁርጠኛ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ እና ባንኩ ዋና ዋና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በሆኑት ኢነርጂ፣ትራንስፖርት እና ሌሎች ዘርፎች የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ በሚያስችላቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ተስማምተዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከስዊድን እና ሩሲያ ማዕከላዊ ባንኮች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኝነቱን ገለጸ
Oct 18, 2025 63
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከስዊድን እና ሩሲያ ማዕከላዊ ባንኮች ጋር በተለያዩ መስኮች ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰራ አስታወቀ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ይገኛል። በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓመታዊ ስብሰባው ላይ እየተሳተፈ ነው። ልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናትን አካቷል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከስብሰባው ጎን ለጎን ከስዊድን እና ሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከስዊድን ማዕከላዊ ባንክ ምክትል ገዥ አና ሴም ጋር የቴክኒክ ትብብር እና ተቋማዊ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። የሞኒተሪ ፖሊሲ ቀረጻ እና ትግበራ፣የፋይናንስ መረጋጋት፣ የብሄራዊ ባንክ የኮሙኒኬሽን ሂደት፣ የክፍያ ስርዓቶች ልማት እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የውይይቱ አጀንዳዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች በእውቀት ሽግግር፣በተቋማዊ አቅም ግንባታ እና ጥናት ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ቀረጻ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ኢትዮጵያ በቀጣይ በብሪክስ ጉባኤዎች ላይ የሚኖራትን ተሳትፎ ላይ ያተኮረ ነው። ኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ልማት፣ማዕከላዊ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ግምጃ ቤት (የሰነዶች ካዝና) ትስስር፣ድንበር ተሻጋሪ ንግድ እና የክፍያ ስርዓትን ማዘመን ላይ ትኩረታቸውን ያደረጉ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ውይይቶች ላይ ያላትን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቶታል። የኢትዮጵያ እና ሩሲያ ብሄራዊ ባንኮች ተከታታይ ውይይቶችን ለማድረግ እና በብሪክስ ማዕቀፍ ትብብር መፍጠር የሚችሉባቸውን እድሎችን ለመመልከት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ውይይቶቹ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ለማጠናከር፣የፖሊሲ ቅንጅትን ለማሳደግ እንዲሁም የባንኩ ሪፎርሞች በማዕከላዊ ባንክ እና የፋይናንስ አስተዳደር ያሉ ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮች ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የልማት ሥራዎች የምታደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋገጠች
Oct 18, 2025 70
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡- እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የልማት እና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ሥራዎች የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ ለመቀጠል ቁርጠኛ መሆኗን አረጋገጠች። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከእንግሊዝ የዓለም አቀፍ ልማት እና አፍሪካ ሚኒስትር ዴዔታ ባሮነስ ጄኒ ቻፕማን ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ዛሬ በሚጠናቀቀው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብሰባ ጎን ለጎን የተካሄደ ነው። በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓመታዊ ስብስባው ላይ እየተሳተፈ ነው። በውይይታቸውም፥ የኢትዮጵያና እንግሊዝን ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች በይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። እንግሊዝ በጤና፣ትምህርት፣ኢነርጂ፣ማኑፋክቸሪንግ፣የገቢ አሰባሰብን ለማዘመን የሚያግዙ ቴክኒካል ድጋፎችን ጨምሮ በሌሎችም ዘርፎች እያደረገች ያለውን ድጋፍ በይበልጥ እንድታሳድግ አቶ አሕመድ ጠይቀዋል። ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሂደት ያደነቁት ባሮነስ ቻፕማን በበኩላቸው፤እንግሊዝ የኢትዮጵያን የልማትና የኢኮኖሚ ዕድገት ለሚያሳልጡ ተግባራት ድጋፏን አጠናክራ ለመቀጠል ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።

Pulse Of Africa

POA English

POA English

Pulse Of Africa - English Language

Your news, current affairs and entertainment channel

Join us on

POA Arabic

POA Arabic - عربي

Pulse Of Africa - Arabic Language

قناتكم الاخبارية و الترفيهية

Join us on

ፖለቲካ
በክልሉ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን የሚከናወኑ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 18, 2025 50
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን ከሚዲያው ጋር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ዛሬ ባካሄደው የሴክተር ጉባኤ ላይ የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አሸናፊ ኤልያስ እንደገለጹት፤ በክልሉ የልማት ዕቅዶችን ወደተግባር በመቀየር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራ ውጤት እየተገኘ ነው። የልማት ግቦች ወደህዝብ ሰርጸው በእኔነት ስሜት እንዲሳተፍባቸውና ተጨባጭ ውጤት እንዲመጣ ሚዲያው የጎላ ሚና ሲጫወት መቆየቱን አስታውሰዋል። በቀጣይም ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶች ላይ በማትኮር የህዝብን አንድነት ለማጠናከር፣ የልማት ሥራዎችን ለመፋጠንና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ገልጸው፤ ለዚህም ከሚዲያው ጋር በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የክልሉ መንግስት ለዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ወሰንየለህ ስምኦን፤ ባለፉት ጊዜያት በዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች አተገባበር ላይ ሚዲያን ያሳተፈ ሥራ በመሰራቱ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። ይህም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የልማት ዘርፎች እየተመዘገቡ ላሉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አቅም እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። ቢሮው በክልሉ ያሉ የልማት አቅሞች እና ባህላዊ እሴቶች በአግባቡ እንዲተዋወቁና እንዲለሙ እንዲሁም የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ያዕቆብ እንዳሉት፣ ቢሮው በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን በመጠቀም የዜጎች የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ ነው። በተለይ ለክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ የተሰጠው ትኩረት በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቅሰው፣ ይህም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በመድኩ በክልሉ ከሚዲያው ዘርፍ ጋር በተቀናጀ መንገድ በመስራት እየተመዘገበ ላለው ውጤት አበርቶ ላላቸው አካላት ዕውቅና ተሰጥቷል።
ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ ነው
Oct 18, 2025 73
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑ ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን 11ኛው ጣና ፎረምን ለማካሄድ በተደረጉ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። 11ኛው ጣና ፎረም ከጥቅምት 14 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድም ተገልጿል።   ፎረሙ "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እና ባህር ዳር ለሶስት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን፤በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። በፎረሙ ላይ የአፍሪካ አገሮች መሪዎች እና ባለድርሻ አካላት በመገኘት በአፍሪካ የደህንነት ችግሮችና አፍሪካዊ መፍትሔዎች ዙሪያ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን የሚያካፍሉበት መርሃ ግብር መዘጋጀቱም ተገልጿል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ 11ኛው የጣና ፎረም በከፍተኛ ደረጃ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል። በአሁኑ ወቅት ዓለም በርካታ ለውጦች እያስተናገደች መሆኑን ገልጸው፤ አፍሪካ ''በምን መልኩ ዕድሎችን ትጠቀማለች? እንዴትስ አትራፊ መሆን ትችላለች?'' የሚለው ርዕሰ ጉዳይ ዋነኛ የፎረሙ ማጠንጠኛ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፎረሙ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ምክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር ያካተተ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች እንደሚወያዩም አብራርተዋል። ጣና ፎረም ለሌሎች አህጉራዊ መድረኮችም እንደ እርሾ ሆኖ አገልግሏል ያሉት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ በፎረሙ እንደመፍትሄ የሚነሱ ሀሳቦች ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ መርህን የተከተለ መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ አኳያ በአፍሪካ አገራት መካከል የጋራ አጀንዳዎች በመቅረጽና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማመላከት አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አስረድተዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ሜርሲ ፍቃዱ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) በበኩላቸው፤ የጣና ፎረም የፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች እየፈለቁበት መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ ከአፍሪካ ውጪም ተሳታፊዎችን የሚጋብዝ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም አጋርነት እንዲጠናከር ትልቅ ሚን እየተጫወተ ነው ብለዋል።
በአካባቢያችን ለሚከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 17, 2025 131
ጂንካ፤ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ) :- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመመለስ እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የክትትልና ድጋፍ ስራቸውን እንደሚያጠናክሩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በጂንካ ከተማ ተካሄዷል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት በአካባቢያቸው እየተከናወኑ ለሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። የዲላ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማ አስተዳደር ምክትል አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ጂግሶ፤ መንግስት የከተማውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።   በከተማው የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለስራ ዕድል ፈጠራ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረው የልማት ስራዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድጋፍና ክትትል ተግባራቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚያሸጋግሩ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ዶቦ አዊኖ ናቸው።   የደቡብ ኦሞ ዞን ዝናብ አጠር ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ መሆኑን የገለፁት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ፤ አርብቶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በመስኖ ልማት እንዲሰማራ መንግስት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚተገበሩ የግብርና ልማት ስራዎች የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የአርብቶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር አማካሪ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ታጋይ ፍላቴ፥ በአካባቢው እምቅ የግብርና አቅም እንዳለ ጠቅሰው በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ ማልማት የሚያስችል ምቹ የአየር ጠባይ እና በቂ የውሃ ሀብት አለ ብለዋል።   እነዚህን አቀናጅቶ በማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመለወጥ እየተሰራ ያለው አበረታች ስራ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በአካባቢው ስንዴና ገብስን የመሳሰሉ ሰብሎች በኩታ ገጠም በስፋት እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው፥ ምርቱን ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። በአካባቢው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚያስችሉ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የኮንሶ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ገልገሎ ኦቶማ ናቸው።   በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ጠቅሰው፥ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ውጤት ማምጣት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በዞኑ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው የህዝቡን አዳጊ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ከግብ እንዲደርስ ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች  የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው
Oct 17, 2025 129
ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አመለከተ። የደብረ ብርሃን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13 ዓመት 47ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።   የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መንግስቱ ቤተ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው። በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በማምረት ገበያን የማረጋጋት ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል። የንግድና ገበያ ማዕከላት ግንባታ ስራዎች ዘመናዊ የግብይት ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል። እነዚህና ሌሎች ተግባራት በበጀት ዓመቱ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ መጓደል ችግሮችን በተደራጀ አግባብ በመፍታት ለህዝቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል። የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ግብርን አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ዕቅድ በጥራትና በተደራሽነት መተግበር እንደሚገባም አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ ባለፉት ወራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወኑ የልማትና ሰላምን የማረጋገጥ ተግባራት ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።   አሁን ላይም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ የተቋማትን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የማሳደግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም 269 ለሚሆኑ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመስጠት ባሻገር 18 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩ በማስፋት ለ1 ሺህ የቤተሰብ መሪዎች ዘመናዊ ቤቶች እንዲገነቡ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። እንዲሁም ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታና መሰል የልማት ተግባራት በትኩረት ይከናወናሉ ሲሉም አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ጉባኤውን በነገው ዕለት እንደሚያጠናቅቅ ታውቋል።
 ህግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል-  አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Oct 17, 2025 164
ገንዳውሃ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል መንግስት የጀመረው ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በምዕራብ ጎንደር ዞን ከገንዳውሃ፣ መተማ ዮሐንስ ከተማና መተማ ወረዳ ከተውጣጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል።   በመድረኩ ላይ ‎የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላም ለማምጣት መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ጭምር እድሎችን በማመቻቸት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበልም በጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን በመፍታት ሰላማዊ ሕይወት እየኖሩ መሆኑን ገልጸው ፤ በዘረፋና እገታ ተግባራቸው የቀጠሉ ጽንፈኞች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ‎በመሆኑም በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን መንግስት ሕግ የማስከበር እርምጃውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። ‎የመከላከያ ሰራዊት 504ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ሙላው በየነ፤ የመንግስትን የሰላም እድሎች በማይጠቀሙ ፅንፈኞች ላይ ሰራዊቱ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን አረጋግጠዋል።   በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋና ግድያ በመፈፀም የሕዝብን ሰላም እያናጋ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የሚወሰደው ሕግ የማስከበር ተግባር ይቀጥላል ብለዋል። ‎የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሁን መንግሥቱ፤ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት በማስጠበቅ ረገድ ማሕበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ የሕግ ማስከበር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚሕ ረገድ የክልሉ ሕዝብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀው በቀጣይም ድጋፉ እንዳይለይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።   የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ፤ የዞኑን ሰላም ለመጠበቅ ከፌዴራልና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሕም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን አንስተው፤ የሕዝቡ የሰላም ጥረት መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የግጭትና ጦርነት አዙሪት አብቅቶ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል።   ከጦርነት ውድመት እንጂ የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ሁላችንም እንገነዘባለን ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ፤ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የጸጥታ ሃይሉን እናግዛለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታችንን በብቃት እንወጣለን
Oct 17, 2025 216
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት እንደሚወጡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ቃል በመግባት አረጋገጡ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች "ብሔራዊ ጥቅምና የጂኦስትራቴጂ ቁመና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት አካሄደዋል።   በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ እንዳሉት፤ ጋዜጠኞች ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚያስችሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የበለጠ መስራት አለባቸው። የወል ትርክትን ለመገንባትና የሀገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን በመስራት ሙያዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።   ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁ የቀደመውን ትርክት መቀየር ያስቻለ መሆኑን አንስተው፤ የኢትዮጵያን የነገ መስመር የሚቀይሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ህዝብና ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላት ሃገር ብትሆንም የባህር በር እንደሌላት አንስተው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት በምታደርገው ጥረት ሙያዊ ሀላፊነታቸውን በብቃት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል።   ኢትዮጵያ ያላትን ተሰሚነትና ተፅዕኖ ፈጣሪነት ለማረጋገጥ የኢዜአ ሰራተኞች ከዜግነት በተጨማሪ ሙያዊ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ነጋሲ አምባዬ የውይይት ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በድህረ እውነት ዘመን የአገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ ዘመኑን በሚመጥን ደረጃ ሙያዊ ሃላፊነትን በሚገባ መወጣት ያስፈልጋል።   ብሔራዊ ጥቅም የሀገር ህልውና ደህንነት እና ብልፅግና ጉዳይ መሆኑን ጠቁመው፤ የብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና የህዝብና የትውልድ አጀንዳ ለማድረግ የበኩላችንን ሚና ልንወጣ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ የማንሰራራት ምዕራፍ ላይ ያለች እና ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኗን ያነሱት ደግሞ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተፈራ በቀለ ናቸው። ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ስራዎችን መስራት ከመገናኛ ብዙሃን የሚጠበቅ መሆኑንም ነው የገለፁት።   የኢዜአ ሰራተኞች በበኩላቸው በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች እንዲሳኩና የጋራ ትርክትን ለመገንባት የበኩላቸውን ሚና አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው
Oct 17, 2025 121
ጭሮ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ አድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ተሰሚነቷን ለማጉላት በዲፕሎማሲው መስክ መንግስት በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል። በዚህ ረገድ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፖለቲካና ዲፕሎማሲው መስክ እንዲሁም ሀገራዊ የምጣኔ ሃብት እድገት እንዲያንሰራራ የሚያደርጉት ጥረት በብዙ መልኩ ይነሳል። ከዙሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ፣ ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን የመገንባት ጅማሮና ኢትዮጵያ የባህር በር እንዲኖራት በመንግስት የተያዘው ጠንካራ አቋም በሁላችንም የሚደገፍ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲው የሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ አስተባባሪ የሆኑት ፈቃዱ ወርቁ፤ የመንግስት የዲፕሎማሲና የሀገር ሁለንተናዊ የልማት ጥረት የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የመልማት ፍላጎት እና ብሄራዊ ጥቅም በማንኛውም የውጭ ጫና የማይቀለበስ እንደሆነ የታየበት መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር ተነጥላ ብትቆይም ከዚህ በኋላ ያለ ባህር በር መዝለቅ የማትችል መሆኑን አጽንኦት በመስጠት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስረዳት እየተሄደበት ያለው ርቀት ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል። የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም ለማሟላት በሚያደርገው ጥረት የምሁራን ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ በጥናትና ምርምር እና በተያያዥ ስራዎች ለሀገር ብልጽግና የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከመቸውም ግዜ በበለጠ ባሉት አማራጮች ሁሉ ኢትዮጵያ ላይ የዘመቱት ሀገሪቱ ማንሰራራት በመጀመሯ በመሆኑ ይህንን በመረዳት ሁላችንም ለሀገራችን ብሄራዊ ጥቅም በጋራ መቆም አለብን ብለዋል። ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጋር በሚጻረር መልኩ በግብጽ በኩል የሚሰነዘሩ አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በጠንካራ ዲፕሎማሲ መመከት እንደሚገባም ነው የገለጹት። በቅርቡ አንድ የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣን በሰጡት አስተያየት ላይ የውሀ እና ኢነርጂ ሚንስቴር ያወጣው መግለጫ ትክክለኛና የኢትዮጵያን አቋም በግልጽ ያሳየ መሆኑን በማከል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የህግ ትምህርት ቤት ዲን ዘከርያ አብዱረህማን በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት የልማት እቅዶችን ከማሳካት ጎን ለጎን በባህር በር ላይ የያዘው ጽኑ አቋም የሚደገፍ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እየገነባች ባለው ከፍተኛ ኢኮኖሚ እና እየጨመረ ባለው የህዝብ ብዛት የተነሳ የባህር በር አልባ ሆና መቀጠል አትችልም፣ ለዚህም ለመንግስት ቁርጠኛ አቋም ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ጠንካራ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በኩል ለሚሰነዘሩ አፍራሽ አጀንዳዎች መንግስት በዲፕሎማሲያዊ ጥብበ መመከቱን መቀጠል እንዳለበትም አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ እና በዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ ነው
Oct 17, 2025 150
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እና ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑን የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የኅልውና ጉዳይ መሆኑንም ነው በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ለኢዜአ የተናገሩት። ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑንም በአጽንኦት አንስተዋል። እስካሁን ባለው ሂደትም በብዙ መመዘኛዎች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እንዳለው መገንዘባቸውን ገልጸዋል። ለውጤታማነቱም ኢትዮጵያ ያላትን ሕጋዊ መሠረት፣ ታሪካዊና የሠነድ ማስረጃ በመጠቀም በሰላማዊ የዲፕሎማሲ ልዕልና ስልት ጥረቷን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅባትም መክረዋል። ለዚህም አጋዡ መሣሪያ ለጎረቤት ሀገራት፣ ለአፍሪካ ኅብረት፣ ለምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለሥልጣን(ኢጋድ)፣ ለዓለም አቀፍ ተቋማትና ተጽዕኖ ፈጣሪ የጋራ ዕድገት ደጋፊ ሀገራት የአቋሟን ትክክለኛነት በልኩ ማስገንዘብ መሆኑን አስረድተዋል። የባሕር በር ለተሻለ ሁለንተናዊ ዕድገት ቁልፍ መሆኑን አስገንዝበው፤ ከሕግና ከሕዝብ ፍላጎት ውጭ በሆነ መንገድ እንድታጣ የተደረገችውን የባህር በር ማግኘት እንደሚገባትም ነው የተናገሩት።
ፖለቲካ
በክልሉ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን የሚከናወኑ ተግባራት ይጠናከራሉ
Oct 18, 2025 50
ሀዋሳ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶችን በማስረጽ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ለማጎልበትና ልማትን ለማፋጠን ከሚዲያው ጋር የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ገለጸ። ቢሮው ዛሬ ባካሄደው የሴክተር ጉባኤ ላይ የክልሉ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አሸናፊ ኤልያስ እንደገለጹት፤ በክልሉ የልማት ዕቅዶችን ወደተግባር በመቀየር የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በተሰራው ሥራ ውጤት እየተገኘ ነው። የልማት ግቦች ወደህዝብ ሰርጸው በእኔነት ስሜት እንዲሳተፍባቸውና ተጨባጭ ውጤት እንዲመጣ ሚዲያው የጎላ ሚና ሲጫወት መቆየቱን አስታውሰዋል። በቀጣይም ገዥና አሰባሳቢ ትርክቶች ላይ በማትኮር የህዝብን አንድነት ለማጠናከር፣ የልማት ሥራዎችን ለመፋጠንና ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ገልጸው፤ ለዚህም ከሚዲያው ጋር በቅንጅት የሚሰሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። የክልሉ መንግስት ለዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ ወሰንየለህ ስምኦን፤ ባለፉት ጊዜያት በዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች አተገባበር ላይ ሚዲያን ያሳተፈ ሥራ በመሰራቱ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል። ይህም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የልማት ዘርፎች እየተመዘገቡ ላሉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አቅም እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል። ቢሮው በክልሉ ያሉ የልማት አቅሞች እና ባህላዊ እሴቶች በአግባቡ እንዲተዋወቁና እንዲለሙ እንዲሁም የህዝብ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ያዕቆብ እንዳሉት፣ ቢሮው በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን በመጠቀም የዜጎች የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ ነው። በተለይ ለክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ የተሰጠው ትኩረት በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ጠቅሰው፣ ይህም ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በመድኩ በክልሉ ከሚዲያው ዘርፍ ጋር በተቀናጀ መንገድ በመስራት እየተመዘገበ ላለው ውጤት አበርቶ ላላቸው አካላት ዕውቅና ተሰጥቷል።
ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ ነው
Oct 18, 2025 73
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ጣና ፎረም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ ለሚለው መርህ ተግባራዊነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑ ተገለጸ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን 11ኛው ጣና ፎረምን ለማካሄድ በተደረጉ ዝግጅቶች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል። 11ኛው ጣና ፎረም ከጥቅምት 14 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድም ተገልጿል።   ፎረሙ "አፍሪካ በተለዋዋጩ የዓለም ሥርዓት" በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እና ባህር ዳር ለሶስት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን፤በአፍሪካ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። በፎረሙ ላይ የአፍሪካ አገሮች መሪዎች እና ባለድርሻ አካላት በመገኘት በአፍሪካ የደህንነት ችግሮችና አፍሪካዊ መፍትሔዎች ዙሪያ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን የሚያካፍሉበት መርሃ ግብር መዘጋጀቱም ተገልጿል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ዘሪሁን አበበ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ 11ኛው የጣና ፎረም በከፍተኛ ደረጃ ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል። በአሁኑ ወቅት ዓለም በርካታ ለውጦች እያስተናገደች መሆኑን ገልጸው፤ አፍሪካ ''በምን መልኩ ዕድሎችን ትጠቀማለች? እንዴትስ አትራፊ መሆን ትችላለች?'' የሚለው ርዕሰ ጉዳይ ዋነኛ የፎረሙ ማጠንጠኛ መሆኑን ጠቅሰዋል። ፎረሙ በመሪዎችና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ምክክር የሚደረግበት መርሃ ግብር ያካተተ መሆኑን ገልጸው፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ልዩ መልዕክተኞች እንደሚወያዩም አብራርተዋል። ጣና ፎረም ለሌሎች አህጉራዊ መድረኮችም እንደ እርሾ ሆኖ አገልግሏል ያሉት ዳይሬክተር ጀነራሉ፤ በፎረሙ እንደመፍትሄ የሚነሱ ሀሳቦች ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ መርህን የተከተለ መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ አኳያ በአፍሪካ አገራት መካከል የጋራ አጀንዳዎች በመቅረጽና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማመላከት አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አስረድተዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሰላምና ደህንነት ጥናት ተቋም ዳይሬክተር ሜርሲ ፍቃዱ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) በበኩላቸው፤ የጣና ፎረም የፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች እየፈለቁበት መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ ከአፍሪካ ውጪም ተሳታፊዎችን የሚጋብዝ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህም አጋርነት እንዲጠናከር ትልቅ ሚን እየተጫወተ ነው ብለዋል።
በአካባቢያችን ለሚከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት ክትትልና ድጋፋችንን እናጠናክራለን-የምክር ቤት አባላት
Oct 17, 2025 131
ጂንካ፤ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ) :- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብን የልማት ጥያቄ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመመለስ እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የክትትልና ድጋፍ ስራቸውን እንደሚያጠናክሩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት ተናገሩ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም በጂንካ ከተማ ተካሄዷል። ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤት አባላት በአካባቢያቸው እየተከናወኑ ለሚገኙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ውጤታማነት የሚያደርጉትን ድጋፍና ክትትል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል። የዲላ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተማ አስተዳደር ምክትል አፈ-ጉባኤ አለማየሁ ጂግሶ፤ መንግስት የከተማውን ህዝብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።   በከተማው የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ ለስራ ዕድል ፈጠራ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረው የልማት ስራዎቹ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የድጋፍና ክትትል ተግባራቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የሚያሸጋግሩ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለፁት ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ዶቦ አዊኖ ናቸው።   የደቡብ ኦሞ ዞን ዝናብ አጠር ከሆኑ አካባቢዎች አንዱ መሆኑን የገለፁት ምክትል አፈ-ጉባኤዋ፤ አርብቶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ በመስኖ ልማት እንዲሰማራ መንግስት ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚተገበሩ የግብርና ልማት ስራዎች የአርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የአርብቶ አደሩን ኑሮ እየለወጠ እንደሚገኝ ተናግረዋል። በአሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር አማካሪ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ታጋይ ፍላቴ፥ በአካባቢው እምቅ የግብርና አቅም እንዳለ ጠቅሰው በአካባቢው ዓመቱን ሙሉ ማልማት የሚያስችል ምቹ የአየር ጠባይ እና በቂ የውሃ ሀብት አለ ብለዋል።   እነዚህን አቀናጅቶ በማልማት የአርሶ አደሩን ኑሮ ለመለወጥ እየተሰራ ያለው አበረታች ስራ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን የተጠናከረ የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በአካባቢው ስንዴና ገብስን የመሳሰሉ ሰብሎች በኩታ ገጠም በስፋት እየለሙ መሆኑን ጠቅሰው፥ ምርቱን ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም አስረድተዋል። በአካባቢው ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የሚያስችሉ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ የኮንሶ ዞን ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ገልገሎ ኦቶማ ናቸው።   በዞኑ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውን ጠቅሰው፥ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመረው ስራ ውጤት ማምጣት መጀመሩን ጠቅሰዋል። በዞኑ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው የህዝቡን አዳጊ ፍላጎት ለማሟላት መንግስት እያደረገ ያለው ጥረት ከግብ እንዲደርስ ምክር ቤቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች  የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው
Oct 17, 2025 129
ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ መሆናቸውን የአስተዳደሩ ምክር ቤት አመለከተ። የደብረ ብርሃን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 13 ዓመት 47ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።   የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መንግስቱ ቤተ እንዳሉት፤ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የሰላምና የልማት ስራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ናቸው። በኢንዱስትሪና በኢንቨስትመንት ዘርፉ ተኪ ምርቶችን በማምረት ገበያን የማረጋጋት ተግባራት የሚበረታቱ ናቸው ብለዋል። የንግድና ገበያ ማዕከላት ግንባታ ስራዎች ዘመናዊ የግብይት ስርዓት ለመዘርጋት አይነተኛ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል። እነዚህና ሌሎች ተግባራት በበጀት ዓመቱ ሰላምን ከማፅናት ባሻገር የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ መጓደል ችግሮችን በተደራጀ አግባብ በመፍታት ለህዝቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ይገባል ብለዋል። የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ግብርን አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ዕቅድ በጥራትና በተደራሽነት መተግበር እንደሚገባም አመልክተዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንዳሉት፤ ባለፉት ወራት ህብረተሰቡን በማሳተፍ በተከናወኑ የልማትና ሰላምን የማረጋገጥ ተግባራት ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።   አሁን ላይም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ፣ የተቋማትን የመፈፀምና የማስፈፀም አቅም የማሳደግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል። በተያዘው በጀት ዓመትም 269 ለሚሆኑ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከመስጠት ባሻገር 18 አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በከተማው የተከናወነውን የኮሪደር ልማት ወደ ገጠሩ በማስፋት ለ1 ሺህ የቤተሰብ መሪዎች ዘመናዊ ቤቶች እንዲገነቡ እንደሚደረግም ጠቁመዋል። እንዲሁም ሁለት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታና መሰል የልማት ተግባራት በትኩረት ይከናወናሉ ሲሉም አብራርተዋል። ምክር ቤቱ ጉባኤውን በነገው ዕለት እንደሚያጠናቅቅ ታውቋል።
 ህግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል-  አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Oct 17, 2025 164
ገንዳውሃ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል መንግስት የጀመረው ህግ የማስከበር እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) ገለጹ። በምዕራብ ጎንደር ዞን ከገንዳውሃ፣ መተማ ዮሐንስ ከተማና መተማ ወረዳ ከተውጣጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር በሰላም፣ በልማትና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል።   በመድረኩ ላይ ‎የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕርግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፤ በክልሉ ሰላም ለማምጣት መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ጭምር እድሎችን በማመቻቸት ብዙ መስራቱን አንስተዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ በመቀበልም በጫካ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን በመፍታት ሰላማዊ ሕይወት እየኖሩ መሆኑን ገልጸው ፤ በዘረፋና እገታ ተግባራቸው የቀጠሉ ጽንፈኞች መኖራቸውን ጠቁመዋል። ‎በመሆኑም በክልሉ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን መንግስት ሕግ የማስከበር እርምጃውን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል። ‎የመከላከያ ሰራዊት 504ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴየር ጄኔራል ሙላው በየነ፤ የመንግስትን የሰላም እድሎች በማይጠቀሙ ፅንፈኞች ላይ ሰራዊቱ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን አረጋግጠዋል።   በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች ዘረፋና ግድያ በመፈፀም የሕዝብን ሰላም እያናጋ ያለው ጽንፈኛ ቡድን ላይ የሚወሰደው ሕግ የማስከበር ተግባር ይቀጥላል ብለዋል። ‎የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሁን መንግሥቱ፤ የሕዝቡን ሰላምና ደሕንነት በማስጠበቅ ረገድ ማሕበረሰቡን ባሳተፈ መልኩ የሕግ ማስከበር ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል። በዚሕ ረገድ የክልሉ ሕዝብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያሳየውን ቀና ትብብር አድንቀው በቀጣይም ድጋፉ እንዳይለይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።   የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ፤ የዞኑን ሰላም ለመጠበቅ ከፌዴራልና ከክልል ፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሕም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም መስፈኑን አንስተው፤ የሕዝቡ የሰላም ጥረት መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም የግጭትና ጦርነት አዙሪት አብቅቶ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የድርሻችንን ለመወጣት ተዘጋጅተናል ብለዋል።   ከጦርነት ውድመት እንጂ የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ሁላችንም እንገነዘባለን ያሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ፤ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የጸጥታ ሃይሉን እናግዛለን ሲሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታችንን በብቃት እንወጣለን
Oct 17, 2025 216
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን በብቃት እንደሚወጡ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች ቃል በመግባት አረጋገጡ። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች "ብሔራዊ ጥቅምና የጂኦስትራቴጂ ቁመና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት አካሄደዋል።   በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሰይፈ ደርቤ እንዳሉት፤ ጋዜጠኞች ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ሕብረ ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚያስችሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የበለጠ መስራት አለባቸው። የወል ትርክትን ለመገንባትና የሀገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎችን በመስራት ሙያዊ ሃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል።   ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁ የቀደመውን ትርክት መቀየር ያስቻለ መሆኑን አንስተው፤ የኢትዮጵያን የነገ መስመር የሚቀይሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆናቸውንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ በርካታ ህዝብና ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላት ሃገር ብትሆንም የባህር በር እንደሌላት አንስተው፤ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት በምታደርገው ጥረት ሙያዊ ሀላፊነታቸውን በብቃት መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል።   ኢትዮጵያ ያላትን ተሰሚነትና ተፅዕኖ ፈጣሪነት ለማረጋገጥ የኢዜአ ሰራተኞች ከዜግነት በተጨማሪ ሙያዊ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ነጋሲ አምባዬ የውይይት ጽሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በድህረ እውነት ዘመን የአገር ብልፅግናን ለማረጋገጥ ዘመኑን በሚመጥን ደረጃ ሙያዊ ሃላፊነትን በሚገባ መወጣት ያስፈልጋል።   ብሔራዊ ጥቅም የሀገር ህልውና ደህንነት እና ብልፅግና ጉዳይ መሆኑን ጠቁመው፤ የብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና የህዝብና የትውልድ አጀንዳ ለማድረግ የበኩላችንን ሚና ልንወጣ ይገባል ብለዋል። ኢትዮጵያ የማንሰራራት ምዕራፍ ላይ ያለች እና ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እያከናወነች መሆኗን ያነሱት ደግሞ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተፈራ በቀለ ናቸው። ብሔራዊ ጥቅምን የሚያስጠብቁ ስራዎችን መስራት ከመገናኛ ብዙሃን የሚጠበቅ መሆኑንም ነው የገለፁት።   የኢዜአ ሰራተኞች በበኩላቸው በኢትዮጵያ እየተገነቡ ያሉ የልማት ስራዎች እንዲሳኩና የጋራ ትርክትን ለመገንባት የበኩላቸውን ሚና አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና የጋራ ትርክትን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ሙያዊ ኃላፊነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው
Oct 17, 2025 121
ጭሮ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ መሆኑን በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ አድገትና ብልጽግና እውን ለማድረግና ዓለም አቀፍ ተሰሚነቷን ለማጉላት በዲፕሎማሲው መስክ መንግስት በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል። በዚህ ረገድ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፖለቲካና ዲፕሎማሲው መስክ እንዲሁም ሀገራዊ የምጣኔ ሃብት እድገት እንዲያንሰራራ የሚያደርጉት ጥረት በብዙ መልኩ ይነሳል። ከዙሁ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናው ተጽእኖ ፈጣሪ ሀገር በመገንባት ረገድ የመንግስት የዲፕሎማሲ ጥረት የሚደነቅ ነው ብለዋል። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ፣ ሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን የመገንባት ጅማሮና ኢትዮጵያ የባህር በር እንዲኖራት በመንግስት የተያዘው ጠንካራ አቋም በሁላችንም የሚደገፍ ነው ሲሉ ተናግረዋል። በዩኒቨርሲቲው የሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ አስተባባሪ የሆኑት ፈቃዱ ወርቁ፤ የመንግስት የዲፕሎማሲና የሀገር ሁለንተናዊ የልማት ጥረት የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ የመልማት ፍላጎት እና ብሄራዊ ጥቅም በማንኛውም የውጭ ጫና የማይቀለበስ እንደሆነ የታየበት መሆኑንም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ከቀይ ባህር ተነጥላ ብትቆይም ከዚህ በኋላ ያለ ባህር በር መዝለቅ የማትችል መሆኑን አጽንኦት በመስጠት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስረዳት እየተሄደበት ያለው ርቀት ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል። የሀገርን ብሄራዊ ጥቅም ለማሟላት በሚያደርገው ጥረት የምሁራን ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በዚህ ረገድ በጥናትና ምርምር እና በተያያዥ ስራዎች ለሀገር ብልጽግና የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከመቸውም ግዜ በበለጠ ባሉት አማራጮች ሁሉ ኢትዮጵያ ላይ የዘመቱት ሀገሪቱ ማንሰራራት በመጀመሯ በመሆኑ ይህንን በመረዳት ሁላችንም ለሀገራችን ብሄራዊ ጥቅም በጋራ መቆም አለብን ብለዋል። ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ጋር በሚጻረር መልኩ በግብጽ በኩል የሚሰነዘሩ አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን በጠንካራ ዲፕሎማሲ መመከት እንደሚገባም ነው የገለጹት። በቅርቡ አንድ የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣን በሰጡት አስተያየት ላይ የውሀ እና ኢነርጂ ሚንስቴር ያወጣው መግለጫ ትክክለኛና የኢትዮጵያን አቋም በግልጽ ያሳየ መሆኑን በማከል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የህግ ትምህርት ቤት ዲን ዘከርያ አብዱረህማን በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት የልማት እቅዶችን ከማሳካት ጎን ለጎን በባህር በር ላይ የያዘው ጽኑ አቋም የሚደገፍ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ እየገነባች ባለው ከፍተኛ ኢኮኖሚ እና እየጨመረ ባለው የህዝብ ብዛት የተነሳ የባህር በር አልባ ሆና መቀጠል አትችልም፣ ለዚህም ለመንግስት ቁርጠኛ አቋም ሁሉም ሀገር ወዳድ ዜጋ ጠንካራ ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በኩል ለሚሰነዘሩ አፍራሽ አጀንዳዎች መንግስት በዲፕሎማሲያዊ ጥብበ መመከቱን መቀጠል እንዳለበትም አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ እና በዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ ነው
Oct 17, 2025 150
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እና ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑን የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ገልጸዋል። የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ሳይሆን የኅልውና ጉዳይ መሆኑንም ነው በዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-አመራርና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ ጌትዬ ትርፌ(ዶ/ር) ለኢዜአ የተናገሩት። ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት እያደረገች ያለው ጥረት በታሪካዊ ዳራ፣ ሕጋዊ ሠነዶች፣ ተፈጥሯዊ አቀማመጥ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ሕጎች መለኪያ ቅቡልና አሳማኝ መሆኑንም በአጽንኦት አንስተዋል። እስካሁን ባለው ሂደትም በብዙ መመዘኛዎች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት እንዳለው መገንዘባቸውን ገልጸዋል። ለውጤታማነቱም ኢትዮጵያ ያላትን ሕጋዊ መሠረት፣ ታሪካዊና የሠነድ ማስረጃ በመጠቀም በሰላማዊ የዲፕሎማሲ ልዕልና ስልት ጥረቷን በይበልጥ ማጠናከር እንደሚጠበቅባትም መክረዋል። ለዚህም አጋዡ መሣሪያ ለጎረቤት ሀገራት፣ ለአፍሪካ ኅብረት፣ ለምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለሥልጣን(ኢጋድ)፣ ለዓለም አቀፍ ተቋማትና ተጽዕኖ ፈጣሪ የጋራ ዕድገት ደጋፊ ሀገራት የአቋሟን ትክክለኛነት በልኩ ማስገንዘብ መሆኑን አስረድተዋል። የባሕር በር ለተሻለ ሁለንተናዊ ዕድገት ቁልፍ መሆኑን አስገንዝበው፤ ከሕግና ከሕዝብ ፍላጎት ውጭ በሆነ መንገድ እንድታጣ የተደረገችውን የባህር በር ማግኘት እንደሚገባትም ነው የተናገሩት።
ማህበራዊ
የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን የማዘመን ስራ ውጤታማ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ጥረት ወሳኝ ነው
Oct 18, 2025 53
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን ለማዘመን እየተከናወነ ያለውን ተግባር ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት የጋራ ጥረት አስፈላጊ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለፁ። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ሰባተኛውን ሀገር አቀፍ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ዓመታዊ ጉባዔ አካሂዷል።   የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚህ ወቅት እንዳሉት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓትን ለማጠናከር የህግና አሰራር ስርዓቱን የማሻሻል ስራ ተሰርቷል። ከ4 ሺህ በላይ ተቋማት ውል በተገባለት የመድኃኒት ግዢ ውል መፈፀማቸውን አንስተው በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋናውን ጨምሮ 20 ማዕከሎች በዚሁ መሰረት ስራቸውን እያከናወኑ ነው ብለዋል። ይህንን ስራ እስከ ጤና ተቋማት ድረስ ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው የመድኃኒት አቅርቦትን ማዘመን የጋራ ጥረትን የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዓለም ጤና ድርጅት ማቹሪቲ ሌቭል 3 መድረሷ ለዘርፉ ተጨማሪ አቅም መሆኑን አንስተው ወደ ቀጣይ ደረጃ ለማድረስ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ያስፈልጋል ብለዋል። የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ በበኩላቸው የመድኃኒት አቅርቦት ተደራሽነት ላይ የተደረገው ማሻሻያ የተራዘመ የግዢ ሂደት ላይ ለውጥ ማምጣት ማስቻሉን አስረድተዋል። ከተቋማት ጋር ውል የተገባለት አቅርቦት ስርዓት በመፈራረም ወደ ስራ መግባቱን አውስተው በ2017 በጀት ዓመት 68 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የመድኃኒትና ሕክምና ግብዓት መሰራጨቱን ጠቁመዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱልቃድር ገልገሎ እንደገለጹት፤ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማዘመንና የሀገር ወስጥ አምራቾችን ለማበረታታት የሚያስችል ስራ ተከናውኗል። በዚህም የሀገር ውስጥ አምራቾች ድርሻ 41 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው፤ ፈጣንና ተጠያቂነት ያለው ስርዓት ለማጠናከር እንደሚሰራ ተናግረዋል። አገልግሎቱ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው ብለዋል። በጉባኤው የተሳተፉ አካላት የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻል የተከናወኑት ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አብዱልሙኒየም አልበሽር አገልግሎቱ ውል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት አበረታች ውጤት እየተመዘገበበትና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ይሄይስ ስብሃት በበኩላቸው ያገኙት የእውቅና ሽልማት ለበለጠ ስራ የሚያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረዋል። ባለፉት ሶስት ዓመታት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓቱን የሚያዘምኑ ስራዎች መከናወናቸው ለዘርፉ መነቃቃት አስተዋፅኦ ማበርከቱን የተናገሩት ደግሞ የክሊቺ ኢስትሮ ባዮቴክ መድኃኒት ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ዳንኤል ዋቅቶሌ ናቸው። በመድረኩ በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ስርዓት የተሻለ ስኬት እንዲመዘገብ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት እውቅና ተሰጥቷል።  
የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በአሶሳ ከተማ ለህፃናት፣ የእናቶች እና ወጣቶች ክሊኒክ እና የስልጠና ማዕከል ግንባታ ጀመረ
Oct 18, 2025 89
አሶሳ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በአሶሳ ከተማ ለህፃናት፣ የእናቶች እና ወጣቶች ክሊኒክ እና የስልጠና ማዕከል ግንባታ ጀመረ። በግንባታ ማስጀመሪያ ስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ፤ የጤናው ዘርፍ ውጤታማነት ለማረጋገጥ ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር በአሶሳ የሚገነባው የህፃናት፣ የእናቶች እና ወጣቶች ክሊኒክ እና የስልጠና ማዕከልም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ተናግረዋል። በተለይ ባለሙያዎች አስፈላጊውን የሙያ ስልጠና እንዲያገኙና ህብረተሰቡን እንዲያገለግሉ በማድረግ በኩል ማዕከሉ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋልም ነው ያሉት። የኢትዮጵያ ሚድዋይፎች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ሂንሰርሙ ባዩ፤ ማህበሩ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የጤናውን ዘርፍ አገልግሎት የሚያሻሽሉ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። በአሶሳ ከተማ የሚገነባው ክሊኒክ እና የስልጠና ማዕከል የባለሙያዎችን የፈጠራ እና የምርምር አቅምን የሚደግፍ እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የሙያ ማሻሻያ ስልጠና እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል። ማዕከሉ በአጭር ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ዝግጁ መሆኑን ጠቅሰው የክልሉ መንግስት የጤናው ዘርፍ እንዲሻሻል እያደረገ ላለው ሥራ አመስግነዋል።
በፍርድ ቤቶች የተገልጋዮችን እርካታ ያረጋገጠ የዳኝነት አገልግሎትን ማጠናከር ይገባል
Oct 18, 2025 85
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በፍርድ ቤቶች በሕዝብ የታመነና የተገልጋዮችን እርካታ ያረጋገጠ የዳኝነት አገልግሎትን ማጠናከር እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ኢሳ ቦሩ አስታወቁ። የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት ዓመት የእቅድ ውይይት እና የ1ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እንዲሁም የእውቅና ፕሮግራም መድረክ ተካሄዷል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ኢሳ ቦሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት መንግሥት ቀልጣፋ፣ ተደራሽና ውጤታማ አገልግሎት የሚሰጡ የፍትህ ተቋማት እንዲፈጠሩ ሰፊ እና ዘርፈ ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም የፍትህ ተደራሽነትን፣ ጥራትንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለተገልጋዩ ከመስጠት አንጻር አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። በተለይ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሰፊ ሥራ መሠራቱ የፍትህ ተደራሽነትን በማረጋገጥ ከፍተኛ እመርታ እንዲመዘገብ ማድረጉን አመልክተዋል። በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በተከናወኑ ተግባራት የፍትህ ተደራሽነትን በማረጋገጥ፣ ጥራትንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ይበል የሚያሰኝ ውጤት መገኘቱን ምክትል ስብሳቢው ተናግረዋል፡፡ በቀጣይም የበለጠ ውጤታማ ለመሆን እና በሕዝብ የታመነ፣ የተገልጋዮችን እርካታ ያረጋገጠ የዳኝነት ተቋም እንዲኖር በትኩረት መስራት እንደሚገባ አፅነኦት ሰጥተዋል። የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንት ፉአድ ኪያር በበኩላቸው በ2017 በጀት ዓመት ቀልጣፋ፣ ውጤታማ እና ተደራሽ የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል። ከዚህ ውስጥም የዳኝነት አገልግሎት ጫናን ለመቀነስ እንዲቻል በርካታ ረዳት ዳኞች እና ሬጅስትራሮች እንዲሾሙ መደረጉን እንዲሁም ለዳኞች፣ ለጉባዔ ተሿሚዎች እና ለሠራተኞች የሙያ ብቃትን ማሳደግ የሚያስችሉ ስልጠናዎች መሰጠታቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል። ፍርድ ቤቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው የተገልጋዮች እርካታ ጥናት በዓለም አቀፍ የፍርድ ቤት መመዘኛዎች ሰባ ስድስት ነጥብ ሶስት በመቶ እርካታ ማስመዝገቡን አንስተው፣ የሕዝብን አመኔታ ያገኙ የዳኝነት ተቋማትን ለመፍጠር በተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል። የፌሰራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት አሸነፈች አበበ፥ የፍርድ ቤቶችን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ባለፉት ሦስት ወራት መከናወናቸውን ገልጸዋል። በቀጣይም የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመለየት የሕዝቡን እርካታ የሚያረጋግጡ የዳኝነት አገልግሎቶችን ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመዋል። በፕሮግራሙ ላይ ውጤታማ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ዳኞች፣ ረዳት ዳኞች፣ የመዝገብ ቤት ባለሙያዎችን ጨምሮ ለበርካታ ውጤታማ ሠራተኞች እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ታዳጊ ሴቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮች በመፍታት ውጤታማ እንዲሆኑ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ
Oct 18, 2025 37
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ ታዳጊ ሴቶች የሚገጥሟቸውን ችግሮች በመፍታት ውጤታማ እንዲሆኑ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። ሚኒስቴሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ13ተኛ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ8ተኛ ጊዜ የዓለም አቀፍ የታዳጊ ሴቶች ቀንን ''ታዳጊ ሴቶች ላይ መስራት የነገን የተሻለች ሀገር መገንባት ነው’’ በሚል መሪ ሀሳብ አክብሯል። የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሂክማ ኸይረዲን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ለታዳጊ ሴቶች ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም። ታዳጊ ሴቶች በሰው ሰራሽና ተፈጥሮ አደጋዎች ታጋላጭ መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ የትምህርትና የጤና ጨምሮ አስፈላጊው ማህበራዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ መሥራት ከሁላችን ይጠበቃል ብለዋል። ታዳጊ ሴቶች ሙሉ አቅማቸውን ተገንዝበው ለህብረተሰቡ ትርጉም ያለው አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ማስቻል ይጠበቃል ያሉት ወይዘሮ ሂክማ የሚገጥማቸውን መሰናክሎችን አልፈው በሀገር ግንባታ ውስጥ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ማብቃት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። በዚህ ረገድ ሚኒስቴሩ ከአጋር አካላት ጋር በመሆን ታዳጊ ሴቶች አቅማቸው እንዲጎለብት በትምህርት ያደጉና የተለወጡ እንዲሆኑ የማደረግ ስራ በስፋት መስራቱን ተናግረዋል። በቴክኖሎጂ ዙሪያም የፈጠራ አቅማቸውን እንዲያጎለብቱ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ትምህርትን ለሁሉም ታዳጊ ሴቶች ተደራሽ ማድረግ ላይ የሚስተዋሉ ውስንቶችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረገው ርብርብ መቀጠሉን አንስተዋል። በተለይም ታዳጊዎች በመጤ ባህል ሰለባ እንዳይሆኑ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ማድረግ ስብዕናው የተገነባ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለማፍራት ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አመልክተዋል። በታዳጊ ሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል የግንዛቤ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ከዚሁ ጋር ተያይዘው የወጡ ሕጎች ተፈጻሚ እንዲሆኑም በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
ኢኮኖሚ
የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና በዘላቂነት የሚያረጋግጥ ነው - ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)
Oct 18, 2025 10
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት አርሶ አደሩ ዓመቱን በሙሉ በማምረት የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥና የገቢ አቅሙ እንዲጨምር የሚያስችል ፕሮጀክት መሆኑን የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ የሚገኘውን የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክት ዛሬ መርቀዋል። የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) በምርቃቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ለዓመታት ሲባክን የነበረው የወልመል ወንዝ ዛሬ ተመርቆ የአካባቢውን ማህበረሰብ በልማት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የመስኖ ፕሮጀክቱ 20ሺህ የሚሆኑ አባውራዎችን ተደራሽ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።   አራት ዓመታትን የፈጀው የፕሮጀክቱ ግንባታ ስድስት ቢሊዮን ብር ወጪ እንደተረገበትም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከግንባታው ጅማሮ እስከ ፍጻሜው ላደረጉት ያልተገደበ ድጋፍና ላሳዩት በሳል አመራርም ሚኒስትሩ አመስግነዋል። አጠቃላይ ፕሮጀክቱ የውሃ መቀልበሻ ውቅር 33 ኪሎ ሜትር ውሃ ማስቀየሻ የመጀመሪያ ቦይ(ፕራይመሪ ካናል)፣ 47 ኪሎ ሜትር ሁለተኛ ቦይ(ሰከንደሪ ካናል) እና 64 ኪሎ ሜትር ሶስተኛ ቦይ(ቴርሸሪ ካናል) በድምሩ 144 ኪሎ ሜትር የቦይና 30 የውሃ ማጠራቀሚያዎች(ፖንዶችን) ያካተተ መሆኑንም ገልጸዋል። በተጨማሪም 60 ኪሎ ሜትር መጋቢ የመንገድ ስራዎች፣ 50 ብሎኮች የያዘ የግድብ አስተዳደርና ለማህበረሰቡ የተለያዩ አገልግሎቶች የሚሰጥ ማዕከል ያለው መሆኑንም አብራርተዋል። የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ አርሶ አደሮች ዓመቱን ሙሉ እንዲያመርቱ፣ የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡ፣ ለብዙ ዜጎች የስራ ዕድል እንዲፈጠር እንዲሁም የቆላማ አካባቢና የአርብቶ አደር ልማትን እውን እንደሚያደርግ ነው ሚኒስትሩ የገለጹት። በዘላቂነትም የአካባቢው ማህበረሰብ ምርትን በመጨመር የገቢ አቅሙን እንዲያሳድግ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።
የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት እንደሚያጠናክር ገለጸ
Oct 18, 2025 49
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ ለዘላቂ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ አረጋገጠ። የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት አጃይ ቡሻን ፓንዲ ጋር የሁለትዮሽ ትብብሮች ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። በዚሁ ወቅት አቶ አሕመድ እንዳሉት፥ የታዳጊ ሀገራትን የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ለማሳደግ ብሎም ከአየር ንብረት ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስ በፋይናንስ አቅርቦት ላይ በትብብር መሥራት ይገባል። ባንኩ ባለፉት ዓመታት ወሳኝ የሆኑ የመሠረተ ልማት ፍላጎቶችን ለመደገፍ ያደረገውን ጥረትም አድንቀዋል። ኢትዮጵያ ስለምትገነባው ግዙፉ አዲሱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክትም ገለጻ አድርገዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በኢነርጂ ዘርፍ ለሚሠሩ ዋና ዋና ፕሮጀክቶች የባንኩ ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል። አጃይ ቡሻን ፓንዲ በበኩላቸው፤ኢትዮጵያ እያካሄደች ላለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና መንግሥት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ የሰጠውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል። ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከር እና ሀገሪቱ ለዘላቂ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ዕድገት የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ባንኩ ቁርጠኛ መሆኑንም አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ እና ባንኩ ዋና ዋና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በሆኑት ኢነርጂ፣ትራንስፖርት እና ሌሎች ዘርፎች የፋይናንስ ድጋፍ ለማድረግ በሚያስችላቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ተስማምተዋል።
በምርምር ማዕከሉ የቀረበልን የተሻሻለ የጤፍ ዝርያ በመጠቀም ምርታማነታችንን ለማሳደግ በትጋት እየሰራን ነው -አርሶ አደሮች
Oct 18, 2025 60
ሰቆጣ ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡- በሰቆጣ ዝናብ አጠር ግብርና ምርምር ማዕከል የቀረበላቸውን የተሻሻለ የጤፍ ዝርያ በመቀጠም ምርታማነታቸውን ለማሳደግ በትጋት እየሰሩ መሆኑን በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የፃግብጅ ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ። በፃግብጅ ወረዳ በምርምር ማዕከሉ የቀረበና በኩታ ገጠም የለማ ''ቁንጮ'' የተሰኘ የጤፍ ዝርያ እንዲሁም የማሽላ ሰብል ዛሬ በመስክ ተጎብኝቷል። በወረዳው የአሪሸርወ ቀበሌ አርሶ አደር አወጣ ብርሃኑ በወቅቱ በተለይ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በምርምር ማዕከሉ የቀረበላቸው ''ቁንጮ'' የተሰኘ የጤፍ ዝርያን በአንድ ሄክታር መሬት አልምተዋል። ካሁን ቀደም በአካባቢ ዝርያ በሄክታር ከ2 ኩንታል ያልበለጠ ምርት ያገኙ እንደነበር አውስተው፤ በመኸሩ ወቅት የተሻሻለው የ''ቁንጮ'' ዝርያን ማዳበሪያ ተጠቅመው መልማታቸውንና ከዚህም ከ10 ኩንታል ያላነሰ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል። አሁን ላይ የሰብሉ ቁመና በጥሩ እድገት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ምርታማነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ በመንከባከብ ተግተው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። አርሶ አደር ወልደስለሴ ግርማ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ከማዕከሉ ባገኙት የተሻሻለ የጤፍ ዝርያ ሩብ ሄክታር መሬት ማልማት ችለዋል። አካባቢያችን ዝናብ አጠር በመሆኑ ቀደም ሲል በልፋታቸው ልክ ምርት እንደማያገኙ አስታውሰው፤ በምርምር ማዕከሉ የቀረበው ዝርያ ችግርን በመቋቋም የተሻለ ምርት እንደሚስጥ ከባለሙያ ትምህርት ወስደው ምርታማነትን ለማሳደግ ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል። በማዕከሉ የቀረበላቸው የ"ቁንጮ" ጤፍ ዝርያ የተሻለ ምርት በማስገኘት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንደሚያገዝ ከባለሙያ ተረድተው በማልማት ላይ እንደሚገኙ የገለጹት ሌላው አርሶ አደር ሲሳይ አማረ ናቸው። በማዕከሉ የምጣኔ ሃብትና ግብርና ስርፀት ተመራማሪ አደመ ምህረቱ እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ስነ ምህዳርን መሰረት ያደረጉ የቁንጮ ጤፍና ማሽላን ጨምሮ የየተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች እየቀረበ ይገኛል። በብሔረሰብ አስተዳደሩ ዝናብ አጠር በመሆኑ በአነስተኛ የዝናብ ስርጭት ፈጥነው የሚደርሱ ዝርያዎች ሲቀርቡ እንደቆዩ አውስተው፤ በፃግብጅ ወረዳም ''ቁንጮ'' የተሰኘ የጤፍ ዝርያ የማስፋፋት ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህም ማዕከሉ ባደረገው ድጋፍ በወረዳው አሪሸርዋ ቀበሌ 30 አርሶ አደሮች የተሳተፉበት 10 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም ዝርያውን ማልማት መቻሉን ተናግረዋል። ማዕከሉ በአካባቢው የሚስተዋለውን የምግብ ዋስትና እና የስርዓተ ምግብ እጥረት ለማቃለል የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎችን ለአርሶ አደሮች ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። ምርምር ማዕከሉ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እያከናወናቸው ያሉት ተግባራት የሚበረታቱ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ናቸው። የምግብ ዋስትናን ችግር ለማቃለል ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን አንሰተው፤ የተሻሻሉ የሰብል ዝርያዎች ለአርሶ አደሩ የማድረስ ተግባር በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ተናገረዋልል። በጉብኝቱ ላይ በየደረጃው የሚገኙ የብሔረሰብ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ተመራማሪዎችና በልማቱ እየተሳተፉ የሚገኙ አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከስዊድን እና ሩሲያ ማዕከላዊ ባንኮች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኝነቱን ገለጸ
Oct 18, 2025 63
አዲስ አበባ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ከስዊድን እና ሩሲያ ማዕከላዊ ባንኮች ጋር በተለያዩ መስኮች ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰራ አስታወቀ። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ይገኛል። በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በዓመታዊ ስብሰባው ላይ እየተሳተፈ ነው። ልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፍተኛ አማካሪ ተክለወልድ አጥናፉ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናትን አካቷል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከስብሰባው ጎን ለጎን ከስዊድን እና ሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከስዊድን ማዕከላዊ ባንክ ምክትል ገዥ አና ሴም ጋር የቴክኒክ ትብብር እና ተቋማዊ ግንኙነትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። የሞኒተሪ ፖሊሲ ቀረጻ እና ትግበራ፣የፋይናንስ መረጋጋት፣ የብሄራዊ ባንክ የኮሙኒኬሽን ሂደት፣ የክፍያ ስርዓቶች ልማት እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የውይይቱ አጀንዳዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች በእውቀት ሽግግር፣በተቋማዊ አቅም ግንባታ እና ጥናት ላይ የተመሰረተ የፖሊሲ ቀረጻ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል። በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ ኢትዮጵያ በቀጣይ በብሪክስ ጉባኤዎች ላይ የሚኖራትን ተሳትፎ ላይ ያተኮረ ነው። ኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ልማት፣ማዕከላዊ የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ግምጃ ቤት (የሰነዶች ካዝና) ትስስር፣ድንበር ተሻጋሪ ንግድ እና የክፍያ ስርዓትን ማዘመን ላይ ትኩረታቸውን ያደረጉ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ውይይቶች ላይ ያላትን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቶታል። የኢትዮጵያ እና ሩሲያ ብሄራዊ ባንኮች ተከታታይ ውይይቶችን ለማድረግ እና በብሪክስ ማዕቀፍ ትብብር መፍጠር የሚችሉባቸውን እድሎችን ለመመልከት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ውይይቶቹ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ለማጠናከር፣የፖሊሲ ቅንጅትን ለማሳደግ እንዲሁም የባንኩ ሪፎርሞች በማዕከላዊ ባንክ እና የፋይናንስ አስተዳደር ያሉ ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮች ጋር የተጣጣሙ እንዲሆኑ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
ቪዲዮዎች
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሸገር ከተማ ለተገልጋዮች ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል
Oct 18, 2025 58
ሸገር፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በሸገር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንግልትን በማስቀረት ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ተገልጋዮች ተናገሩ። በሸገር ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ከተመዘገቡት ከ11ሺህ 224 ተገልጋዮች አብዛኞቹ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘታቸውን እንደገለጹም ተመላክቷል። ከተጠቃሚዎቹ መካከል በአስተዳደሩ የፉሪ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሁዳ አብዱልከሪም፤ በአሁኑ ወቅት በማዕከሉ እያገኙት ያለው አገልግሎት በእጅጉ መሻሻሉን ለኢዜአ ተናግረዋል። ከዚህ በፊት አገልግሎት ለማግኘት ውጣ ውረድ ብሎም ላልተገባ ወጪ ሲዳረጉ እንደነበር አውስተው፤ አሁን ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚፈልጉትን አገልግሎት በማግኘት ምቹ ሁኔታ አንደተፈጠረላቸው ገልጸዋል። ቀደም ሲል በነበረው አገልግሎት ፋይል የመጥፋት አጋጣሚና ሌሎችም ችግሮች እንደነበር በማስታወስ አስተያየት የሰጡት ደግሞ ከገላን ክፍለ ከተማ የመጡ አቶ ወርቅነህ በንቲ ናቸው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ አገልግሎት ሰጪ ባለሙያዎቹ መልካም ስነምግባር በመላበስ ከአስር ደቂቃ በታች ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት እንደሚያስተናግዱና በዚህም መደሰታቸውን ተናግረዋል። ሌላው ተገልጋይ ከኩራጅዳ ክፍለ ከተማ የመጡት አቶ ሀብታሙ ጆቴ፤ በከተማው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከተጀመረ ወዲህ ከ15 ደቂቃ ባነሰ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እያገኙ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። የሸገር ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት ኦፕሬሽን ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ካሳሁን ጆብር እንዳሉት፤ ቀደም ሲል በከተማው የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በተበታተነና በተራራቀ መልኩ የሚያካሄዱት አሰራር በቴክኖሎጂ ያልተደገፈና የመረጃ ስርዓቱ ያልተሟላ ነበረ ። አገልግሎቱን ለማሻሻል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በማስጀመር የሚያስፈልጉትን ቴክኖሎጂና የሰው ሃይል በማሟላት ለማሕበረሰቡ ተደራሽ፤ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል። ይህ አሰራር ከተጀመረ በሶስት ወራት ውስጥም ከተመዘገቡት ከ11ሺ224 ሰዎች ውስጥ አስር ሺህ ሰዎች አገልግሎት ማግኘት መቻላቸውን ጠቅሰዋል። በቀጣይ አገልግሎቱን የበለጠ በማስፋፋት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ለባለሙያው የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። ተገልጋዮች የሚጠበቅባቸውን አሟልተው እንዲገኙ ግንዛቤ ከመስጠት ጎን ለጎን በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መመቻቸቱን አስረድተዋል። በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ከሸገር ከተማ በተጨማሪ በቢሾፍቱ፤ አዳማ፤ ሻሸመኔና ጅማ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩ የሚታወስ ነው።
የልህቀት ማዕከሉ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የሚቆም ሚዲያ እና ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተላበሰ ጋዜጠኛ ለመፍጠር ያስችላል
Oct 18, 2025 78
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡- የሚዲያ ልህቀት ማዕከል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የሚቆም ሚዲያ እና ሙያዊ ሥነ ምግባርን የተላበሰ ጋዜጠኛ ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የመገናኛ ብዙኃን ለሀገር ግንባታ፣ ለዜጎች የመረጃ ተደራሽነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ጉልህ ሚና እንዲኖረው የዓለምን ነባረዊ ሁኔታ የዋጀ የዘርፉ ባለሙያ እና ቴክኖሎጂ መታጠቅ አለባቸው፡፡ በኢትዮጵያ ከለውጡ በኋላ የመገናኛ ብዙኃንና ጋዜጠኞች ዘርፉ የሚጠይቀውን ሙያዊ ሥነ ምግባር ተላብሰው ለሀገር ግንባታና ለዜጎች ተደራሽነት በነፃነት መስራት የሚችሉባቸው የህግና የአሰራር ማሻሻያዎች ተደርገዋል፡፡ በቅርቡም የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን ዕውቀትና ክህሎት በምርምር፣ በማማከርና ስልጠና ማሳደግ የሚያስችል የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ሥራ ጀምሯል፡፡ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ አዲስ አበባን ጨምሮ በ25 ዩኒቨርሲቲዎች የጋዜጠኝነት ትምህርት እየተሰጠ ነው፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርቱን መስጠታቸው ትልቅ ነገር መሆኑን ያወሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ሆኖም አብዛኞቹ የጋዜጠኝነት ምሩቃን የንድፈ ሃሳብ እንጂ የተግባር ዕውቀትና ክህሎት እንደሚጎድላቸው ለይተናል ብለዋል፡፡ ጋዜጠኝነት ጽንሰ ሀሳቡን ተረድቶ ትንታኔ መስጠትና ማብራራት ቢሆንም ክፍተት ይታያል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በሥራ ላይ ያሉ ጋዜጠኞች ተለዋዋጭ ከሆነው የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር በየጊዜው መዘመን እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ውስን ዓላማን ብቻ ለማስፈፀም እንደነበር ገልጸው፤ ኢትዮጵያ ምን ዓይነት ጋዜጠኝነት ትፈልጋለች የሚለውን መመለስ የሚያስችል የተቀናጀ ስልጠና አልነበረም ብለዋል፡፡ ጋዜጠኝነት ከዓለም ነባራዊ አውድ ጋር የተጣጣመ ቀጣይነት ያለው ዝማኔ ይፈልጋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የኢትዮጵያ የሚዲያ ልህቀት ማዕከልን ማቋቋም ማስፈለጉን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ኢትዮጵያን የሚመስል ዘመኑን የዋጀ የመገናኛ ብዙኃንና የጋዜጠኝነት ሙያ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ግቡ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና ለሀገር ግንባታ የሚቆም፣ ለዜጎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚተጋ የመገናኛ ብዙኃንና ጋዜጠኛ ማፍራት መሆኑን አንሰተዋል፡፡ በዚህም የልህቀት ማዕከሉ በብቁ የሰው ሀይል እና በቴክኖሎጂ የተሟላ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል ጋዜጠኛውን ብቻ ሳይሆን መገናኛ ብዙኃንን ጭምር እንዲያልቅ እንፈልጋለን ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በጥናትና ምርምር፣ ስልጠናና በማማከር ሀገር በቀል እሳቤዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በዓለም ላይ ጋዜጠኝነት ከጥቅል ወደ ልዩ ዘጋቢነት እየተቀየረ መሆኑን በማስታወስ፤ ጋዜጠኞችን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በምርጫ፣ ውሃ፣ ፋይናንስ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ አቬሽን ጋዜጠኝነትና መሰል ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በማሰልጠንና በማብቃት የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ማዕከሉ የምርጫ ጋዜጠኝነት ስልጠና በቅርቡ እንዲሚጀምር በመጥቀስ፤ ከስድስት ዩኒቨርሲቲዎች በመጡ 32 ፕሮፌሰሮች 11 የሥልጠና ሰነዶች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ ለሶስት ወራት በሚሰጠው የምርጫ ጋዜጠኝነት ሥልጠና የተዘጋጁ ሰነዶች የኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ፣ ሚዲያና ዲሞክራሲ፣ ሚዲያና ብሔራዊ ጥቅም፣ ምርጫና የዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ልምድ፣ እንዲሁም ሚዲያ ማህበረሰብና ባህል የሚሉ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ ይገባል
Oct 18, 2025 67
ጅማ ፤ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፡-የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከር በሚደረገው ሂደት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታወቀ። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር "የሳይበር ደህንነት የዲጂታል ኢትዮጵያ መሰረት" በሚል መሪቃል በጅማ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።   የሳይበር ደህንነት ወርን በማስመልከት በተዘጋጀው በዚህ የውይይት መድረክ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን መድረኩም ግንዛቤ የመፍጠር ዓላማ እንዳለው ተመላክቷል። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ዲጂታል የመንግስት አገልግሎትን ለማስፋፋት ትኩረት ከመስጠት ባለፈ በሳይበር ደህንነት ላይ ጠንካራ ሥራ እየተሰራ ነው። ተቋማቱም የሳይበር ደህንነት ተጋላጭነታቸውን በመቀነስ አስተማማኝ እና ዘመናዊ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ትኩረት መሰጠቱን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል። የዲጂታላይዜሽን አገልግሎት ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የሁልግዜም ተግባር ሊሆን እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። የሳይበር ደህንነትን ወርም ይህን እውን ለማድረግና የሀሰተኛ የመረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር በማለም እንደሚከበር አክለዋል። በተለይም የስማርት ከተማን በመገንባት ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎቶችን ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ የዲጂታል አገልግሎት ጉልህ አስተዋጾ እንዳለው ነው የገለጹት። ለተግባራዊነቱም ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመተባበር የዲጂታላይዜሽን አገልግሎትን ለማጠናከርና የስማርት ከተሞችን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። በብልጽግና ፓርቲ የጅማ ከተማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዋሴ ግርማ በበኩላቸው እንዳሉት በጅማ ከተማ ዲጂታል አገልግሎቶችን በመተግበር ስማርት ከተማ ለመገንባት እየተሰራ ነው። ለእዚህም ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በመተባበር በከተማዋ ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ የተለያዩ ተቋማት የሥራ ሀላፊዎች እንዲሁም የፌደራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸው ታውቋል።  
በአፍሪካ ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ ይገባል
Oct 17, 2025 133
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 7/2018 (ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ ክህሎት ማሳደግ እንደሚገባ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ። ከጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው 2ኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል።   የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) መርሃ ግብሩ፣ በአፍሪካ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠናን ጥራት ለመጠበቅና ተደራሽነቱን ለማስፋት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ምርጥ ተሞክሮ ያካፈለችበት እና ከሌሎች ልምድ የወሰደችበት ስኬታማ መድረክ እንደነበርም ገልጸዋል። የአፍሪካ መጻዒ እድል የሚወሰነው በወጣቶች ላይ በምንሰራው ሁሉን አቀፍ የክህሎት ልማት ስራ ልክ ነው ሲሉም ገልጸዋል። በአፍሪካ ዘላቂና ሁለንተናዊ ልማትን ለማረጋገጥ የወጣቱን የፈጠራና የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግ እንደሚገባም አመላክተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለሰው ሀብት ልማት ስራ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች እንደምትገኝ ጠቁመው፤ በቀጣይም ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ጋር በማስተሳሰር አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታውቀዋል።   በመድረኩ ማጠቃለያም የአፍሪካ አገራት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሀብት ለማፍራት በጋራ የሚሰሩበት አቅጣጫ መቀመጡንም አመላክተዋል። በአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጋስፓርድ ዳንያንክምቦና በበኩላቸው፤ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት የእድገት ማሳለጫ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡   በመሆኑም የአፍሪካ አገራት በአፍሪካ ህብረት 2063 አጀንዳ መሰረት ቅንጅት በመፍጠር ዘርፉን በማሳደግ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማፍራት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡ የዛሬ የአፍሪካ ወጣቶች ነገን ፈጠራ በታከለበት ሁኔታ መምራትና ለውጥ የማምጣት ሃላፊነት እንደተጣለባቸው አንስተው፤በዚህ ሒደት ውስጥ ከጎናቸው እንደሚሆኑ አረጋግጠዋል፡፡ ከኢኳቶሪያል ጊኒ የመጡ የመድረኩ ተሳታፊ ዮላንዳ አሱሙ በበኩላቸው፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የክህሎት ሳምንት በርካታ ልምዶችን የተለዋወጥንበት ነበር ብለዋል፡፡   የአፍሪካ ሁለተኛው ክህሎት ሳምንት እጅግ አስተማሪና ትልቅ ግንዛቤ የወሰድንበት ሆኖ አልፏል ያለው ደግሞ ከሴኔጋል የመጣው ወጣት ደቪድ ሞዓድ ነው፡፡  
ስፖርት
በፕሪሚየር ሊጉ ሲዳማ ቡና ድል ሲቀናው ነጌሌ አርሲ እና አርባምንጭ ከተማ አቻ ተለያይተዋል
Oct 18, 2025 48
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች መካሄዳቸውን ቀጥለዋል። በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲን 4 ለ 1 አሸንፏል። አበባው አጂሶ፣ አስቻለው ሙሴ፣ ተመስገን መንገሻ እና የወልዋሎው ጌታሁን ባፋ በራሱ ላይ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል። ሰመረ ሀፍታይ ለወልዋሎ ብቸኛውን ጎል ከመረብ ጋር አገናኝቷል። ብሩክ እንዳለ በጨዋታው ከወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ በኩል በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። ብሩክ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያውን ቀይ ካርድ የተመለከተ ተጫዋች ሆኗል። አዲስ አዳጊው ነጌሌ አርሲ እና አርባምንጭ ከተማ በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል። ሀቢብ ከማል ለነጌሌ አርሲ፣ ታምራት እያሱ ለአርባምንጭ ከተማ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በሊጉ የመክፈቻ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሸገር ከተማን 1 ለ 0 ማሸነፉ ይታወቃል። ድሬዳዋ ከተማ ከሃዋሳ ከተማ ጋር በአሁኑ ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛል።
አካባቢ ጥበቃ
በአማራ ክልል ከ260 ሺህ ሄክታር በሚልቅ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ሥራ ይከናወናል
Oct 18, 2025 67
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የተቀናጀ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ገለጹ። የአማራ ክልል የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመስኖና የተቀናጀ የተፈጥሮ ሃብት ልማት ስራዎች ንቅናቄ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር በደብረ ብርሃን ከተማ ልቼ ቀበሌ ተካሂዷል።   በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) የተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ካልመጣ የመስኖ ስራ ውጤታማ እንደማይሆን ገልጸዋል። ክልሉ በመስኖ መልማት የሚችል ሰፊ አቅም እንዳለው ተናግረዋል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ በዚህ ዓመት ከ52 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መስኖ በማስገባት የክልሉን የመስኖ ልማት ወደ 383 ሺህ ሄክታር ከፍ ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል። ከተፈጥሮ ሀብት ልማት እና ጥበቃ ስራዎች አንጻርም በዚህ ዓመት ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የአፈር እና ውሃ እቀባ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። ይህንንም ለማድረግ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን የሚሆን የደን እና የፍራፍሬ ችግኝ ልማት እቅድ ተይዞ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን አመላክተዋል። የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ዝግጅቶቹ የመስኖ አውታር ግንባታ፣ የቅየሳ፣ የአርሶ አደሮች ስልጠና እንዲሁም የችግኝ ጣቢያዎች ግንባታ እና የእርሻ መሳሪያ ዝግጅቶችን ያካተተ መሆኑን አንስተዋል። በተደረጉ ጥናቶች ክልሉ በመስኖ ሊለማ የሚችል 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት እንዳለው ገልጸዋል። ይህንን ለማልማትም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ ረገድ ባለፉት ዓመታት በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። በርካታ የውሃ መሳቢያ መሳሪያዎች ወደ ዞኖች እና ወረዳዎች መከፋፈሉን ገልጸው ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል ስራ መሆኑን ገልጸዋል።
ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር ይገባል
Oct 18, 2025 63
አዳማ፤ጥቅምት 8/2018(ኢዜአ)፡-ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብና የአፈርና ውሃ ጥበቃን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ። የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንት በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ዛሬ ተጀምሯል። የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ጌቱ ገመቹ በወቅቱ እንዳመለከቱት፥ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራዎች የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር፣ድርቅና የጎርፍ አደጋዎችን ለመመከት አግዘዋል።   በተለይም በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኖችን የመንከባከቡ ስራ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ለመቋቋምና የተራቆቱ መሬቶች እንዲያገግሙ፣የደረቁ ሃይቆች፣ወንዞችና ዥረቶች ተመልሰው ለመስኖና ለተለያዩ ልማቶች እንዲውሉ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል። በበጋ ወቅት የተገነቡ የተፋሰስ ልማቶችን በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ በመሸፈንና በመንከባከብ ውጤት መገኘቱንም አንስተዋል። ተግባሩንም ለማዝለቅ የችግኝ እንክብካቤ የንቅናቄ ሳምንትን በማወጅ በዛሬው ዕለት የክልሉ ግብርና ሴክተር አመራሮችና ሰራተኞች በምስራቅ ሸዋ ዞን ማስጀመራቸውን ጠቁመዋል። በችግኝ እንክብካቤው አረም በማንሳት፣የመኮትኮትና ውሃን በማጠጣት ችግኞቹ የበጋውን ወቅት እንዲቋቋሙ መስራት ይገባል ብለዋል። በንቅናቄው ማስጀመሪያው መርሃ ግብር ላይ የተሳተፉት ከድር መሐመድ በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ሶስት ዓመታት የተተከሉትን ችግኞች በመንከባከብ እንዲያድጉ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።   ችግኝ መትከል ብቻውን ግብ እንዳልሆነ ተናግረው፤የተተከሉትን ችግኞች በየጊዜው በመንከባከብ ለውጤት እንዲበቁ ማድረግ አለብን ብለዋል። ዘርፌ ማሞ በበኩሏ፥ በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ በቀዳሚነት የሚጎዱት ሴቶች በመሆናቸው ለመፍትሔው ላለፉት ሰባት ዓመታት በችግኝ ተከላና እንክብካቤ ላይ መሳተፋቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ ናት- ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)
Oct 16, 2025 161
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የምስጋና መርኃ ግብር አካሂዷል።   በመርኃ ግብሩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያሥላሴ፣ ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተገኝተዋል። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ ለአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ምላሽ ለመስጠት ያለንን ቁርጠኝነት ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል። ጉባዔው አፍሪካውያን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጨባጭ መፍትሔዎችን በመውሰድ ግንባር ቀደም መሆናቸውን ለዓለም በማሳየት ስኬታማ መሆኑን ተናግረዋል።   በቀጣይም ለጋራ ችግሮች በጋራ ምላሽ ለመስጠት አቅማቸውን ያጠናከሩበት እንደሆነ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ይህን ስኬት ተጠቅሞ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መድረኮች የአፍሪካን መሪነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።  
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት የሥራ ዕድል ፈጠራ ውጤታማ ተግባር እያከናወነች ትገኛለች
Oct 16, 2025 128
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል በአፍሪካ ግንባር ቀደም የሆነ ተግባር እያከናወነች መሆኑ ተገለጸ። ይህ የተገለጸው "አረንጓዴ የሥራ ዕድሎችና ወጣቶች" በሚል ርዕስ በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የተጠና ጥናት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ይፋ በሆነበት መድረክ ላይ ነው።   የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የጥናቱ መሪ ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና እንደገለጹት የአረንጓዴ ልማት ስራ ዕድል ፈጠራ የአካባቢን ዘላቂነት ከማረጋገጥ ባሻገር ለወጣቶች ከፍተኛ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኩል ወሳኝ ሚና አለው። ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የአካባቢ ጥበቃን በማጠናከር ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር በአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነች መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይ በአረንጓዴ ልማት የሚፈጠረውን የሥራ ዕድል በሁሉም ሴክተሮች በማስፋት የወጣቱን የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማትን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል። በመሆኑም በተለይ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የአረንጓዴ የስራ ዕድል የሚፈጥሩ ስልጠናዎች ተገቢ ትኩረት እንዲያገኙ እንዲሁም በፖሊሲዎች ውስጥ ልዩ ትኩረት እንዲሰጣቸው በማድረግ ሊበረታቱ እንደሚገባም አመልክተዋል።   የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አለበል ደሴ በበኩላቸው፣ ጥናቱ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ዕድገት ስትራቴጂዎችና የወጣቶች የሥራ ስምሪት ዕቅዶችን እንደሚደግፍ ጠቅሰዋል። ግኝቶቹ ወደ ተግባራዊ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች እንዲተረጎሙ ከሚመለከታቸው የመንግስት መሥሪያ ቤቶች እና የልማት አጋሮች ጋር በቀጣይ እንደሚሰራበት ተናግረዋል። ኢንስቲትዩቱ የአካባቢ ጥበቃን የሚያጠናክር አረንጓዴ ሥራዎች ሙያዊ ሥልጠና ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ጉዳዮች ዳይሬክተር ገነነ አበበ(ዶ/ር) ናቸው።   በቀጣይ የአረንጓዴ ሥራን ይበልጥ ለማስፋፋት በተለይ በቀጣሪ መሥሪያ ቤቶችና ሌሎች ተቋማት ላይ የግንዛቤ ሥራ ማጠናከር ይገባል ብለዋል።  
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር የጀመራቸውን ጥረቶች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ
Oct 15, 2025 259
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 5/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የገጠር ሴቶችን ኑሮ ለመቀየር እና በአህጉሪቷ የማካካሻ ፍትህን ለማረጋገጥ በበለጠ ቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታወቀ። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን በአፍሪካ ደረጃ ዛሬ በአህጉሪቷ መዲና አዲስ አበባ ዛሬ ይከበራል።   “የገጠር ሴቶችን በማካካሻ ፍትህ አማካኝነት ማብቃት፤ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ስርዓተ ምግብን ማረጋገጥ” የቀኑ መሪ ሀሳብ ነው። በቀኑ አከባበር ላይ የአፍሪካ ህብረት አመራሮች፣ የመንግስታት ተወካዮች፣ የገጠር ሴቶች አመራሮች እና ተወካዮች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ የዳያስፖራ ተወካዮች፣ የልማት አጋሮች እና የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ይሳተፋሉ። የቀኑ አከባበር አካል የሆነ የቴክኒክ ውይይት ትናንት የተካሄደ ሲሆን የአፍሪካ የገጠር ሴቶች መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ባለሙያዎች ሴቶችን ለማብቃት በየሀገራቱ እየተተገበሩ ያሉ ኢኒሼቲቮችን አስመልክቶ የእውቀት እና የተሞክሮ ልውውጥ አድርገዋል። ዛሬ በሚኖረው ዋናው የቀኑ አከባበር የከፍተኛ ባለስልጣናት ቁልፍ ንግግሮች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የገጠር ሴቶች ኢኒሼቲቭ የተሞክሮ ማጋራት መርሃ ግብሮች እና አውደ ርዕዮች ይካሄዳሉ። ሁነቶቹ የገጠር ሴቶች በትምህርት፣ ቴክኖሎጂ እና በግብርና መካናይዜሽን አማካኝነት የሚበቁባቸው የኢኖቬሽን አማራጮች የሚቀርቡባቸው ናቸው። ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን ከአፍሪካ ህብረት የ2025 መሪ ሀሳብ ከሆነው “የማካካሻ ፍትህ ለአፍሪካውያን እና ለዘርዓ አፍሪካውያን” የተሳሳረ መሆኑ ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የማሻሻሻ ፍትህ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል አካሄድ መሆኑን አመልክቷል።   የቀኑን አከባበር ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን የጋራ መግለጫው አፍሪካ ስርዓተ ጾታን ባማከለ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ስራ፣ የገጠር ሴቶችን በማብቃት እንዲሁም ማካካሻ ፍትህ እኩልነት የተረጋገጠበትና የማይበገር ስርዓተ ምግብ ለመገንባት ያላትን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያመላክት እንደሆነ ተገልጿል። የዓለም የገጠር ሴቶች ቀን የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ ጾታ እኩልነት ለማረጋገጥ እና በማካካኛ ፍትህ አማካኝነት በገጠሪቷ የአፍሪካ አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። ህብረቱ ቀኑን ሲያከብር የበለጸገች፣ ሁሉን አቃፊ እና ዘላቂነትን ያረጋገጠች አህጉር ለመገንባት ባለው መሻት ውስጥ ሴቶች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ወደኋላ እንዳይቀሩ ዳግም ቃል ኪዳኑን የሚያድስበት እንደሆነ አመልክቷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እ.አ.አ በ2007 ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ባፀደቀው የውሳኔ ሀሳብ ቁጥር 62/136 አማካኝነት ዓለም አቀፍ የገጠር ሴቶች ቀን እ.አ.አ ኦክቶበር 15 እየተከበረ ይገኛል። ቀኑ በገጠር የሚገኙ ሴቶች ለግብርና፣ ምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና ዘላቂ ልማት ያላቸው ወሳኝ አበርክቶዎች የሚዘከርበት ነው።
የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን በሙሉ አቅም መተግበር ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው - መሐመድ አሊ ዩሱፍ
Oct 10, 2025 400
አዲስ አበባ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ሙሉ ለሙሉ ገቢራዊ ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ገለጹ። 24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ አገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ነው። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ሁነቶች በአፍሪካ የኢኮኖሚ እድገት እና ተወዳዳሪነት ተጽእኖ እያሳደሩ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ይህም ከመቼው ጊዜ በላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ ለሙሉ በአፋጣኝ መተግበር እንደሚገባው የሚያመላክት ነው ብለዋል። ሊቀ መንበሩ የአፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ከቀረጥ ጋር ያልተያያዙ የንግድ ገደቦችን በማንሳት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የተሳለጠ የንግድ ልውውጥ ማድረግ የሚያስችሉ ማዕቀፎችን በመተግበር ለአጀንዳ 2063 መዋቅራዊ ትራንስፎርሜሽን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል። የኮሜሳ፣ የደቡብ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳዴቅ) እና የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ (ኢኤሲ) የሶስትዮሽ ትብብር ማዕቀፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ማዕቀፉ የትስስር አጀንዳ ተምሳሌት እና አንድ የሆነች፣ የበለጸገች እና ራሷን የቻለች አህጉር ለመፍጠር የተጀመረውን ጉዞ የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ መሆኑን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ከቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር ቀጣናዊና አህጉራዊ የትስስር አጀንዳዎችን ትግበራ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደሚሰራ መግለጻቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ኢጋድ እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንደሚያጠናክሩ ገለጹ
Oct 10, 2025 369
አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በፍልሰት አስተዳደር እና አየር ንብረት ለውጥ መከላከል ያላቸውን የቆየ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የበለጠ ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ። ጀርመን ለኢጋድ ቀጣና የተለያዩ የፋይናንስ ድጋፍ ማዕቀፎችንም ይፋ አድርጋለች። የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) እና ጀርመን በልማት ትብብራቸው ዙሪያ በጅቡቲ ስትራቴጂካዊ ምክክር አድርገዋል።   በምክክሩ ላይ የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር)፣ የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ሚኒስቴር የምስራቅ አፍሪካ ዘርፍ ኃላፊ ሃኒንግ እና በጅቡቲ የጀርመን አምባሳደር ሄይከ ፉለር (ዶ/ር) ተገኝተዋል። ስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር የገመገሙ ሲሆን በቀጣይ የግንኙነት ማዕቀፎች ላይም መክረዋል። ፍልሰት እና አየር ንብረት ለውጥ የውይይቱ አበይት ማጠንጠኛዎች ናቸው። ሁለቱ ወገኖች የጀርመን ቀጣናዊ የፍልሰት ፈንድ ዳግም ማዋቀር ሂደት መልካም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በማንሳት የኢጋድ የቀጣናዊ የፍልሰት ፖሊሲ ማዕቀፍ ፣ የነጻ እንቅስቃሴ የህግ ማዕቀፎች እና የዜጎችን የአኗኗር ሁኔታ የማጠናከር ስራ ለመደገፍ የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ጀርመን ለኢጋድ የፍልሰት ፖሊሲ ትግበራ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ ትግበራ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ ቃል መግባቷን ኢዜአ ከቀጣናዊ ተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በተጨማሪም ጀርመን በኢጋድ አባል ሀገራት ለሚከናወኑ የማይበገር የአየር ንብረት ለውጥ አቅም ግንባታ ስራዎች በቀጣናዊ የአደጋ ፋይናንስ ፕሮግራም አማካኝነት 22 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዩሮ ለመደገፍ መዘጋጀቷ ተመላክቷል። የፋይናንስ ማዕቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ድንገተኛ አደጋዎችን የመከላከል ስራዎች የሚደገፍ እና የኢጋድ የድርቅ አደጋን የመቋቋም እና ዘላቂነት ኢኒሼቲቭ ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን የሚደግፍ ነው። በስትራቴጂካዊ ምክክሩ ሁለቱ ወገኖች ውጤት ተኮር፣ አሳታፊ እና ተጠያቂነትን መሰረት ያደረገ አጋርነትን መፍጠር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። ኢጋድ እና ጀርመን ትብብራቸውን ለማጠናከር፣ የጋራ ስራዎቻቸው የአባል ሀገራት የቅድሚያ ትኩረቶች ያማከሉ እንዲሆኑና የፖሊሲ ምክክራቸውን በመደበኛነት ለማከናወን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። ኢጋድ እና ጀርመን 37 ዓመታትን ያስቆጠረ አጋርነት እንዳላቸው መረጃዎች ያመለክታሉ።
የአፍሪካ ህብረት የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል
Oct 7, 2025 441
አዲስ አበባ፤ መስከረም 27/2018 (ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ህብረት የአህጉሪቷ ወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራውን ይበልጥ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን አስታወቀ። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ከፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች ከሆኑት ዲያላ ሞሙኒ እና አህመድ ቤኒንግ ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።   የአፍሪካ ህብረት የወጣቶች ልዩ የቴክኒክ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ኡቺዚ ምካንዳዋየር በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል። የአፍሪካ ህብረት ስምምነቱ የአህጉሪቷ ወጣቶች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና ወጣቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ ገልጿል። በስምምነቱ አማካኝነት የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት በሀገራት ደረጃ ያሉ የወጣት ምክር ቤቶች የሚያቀናጅ አህጉራዊ ማዕቀፍ እና ለአፍሪካ ወጣቶች እንደ ጋራ ድምጽ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። የፓን አፍሪካ የወጣቶች ህብረት የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ንቅናቄ የወለደው አህጉራዊ አደረጃጀት ሲሆን እ.አ.አ በ1962 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በጊኒ ኮናክሪ ባደረጉት ስብስባ ህብረቱን አቋቁመዋል።   ህብረቱ የተመሰረተው በወቅቱ ወጣቶች አፍሪካ ከቅኝ ግዛት እንድትላቀቅ ለነበረው ትግል አቅም እንዲሆኑ ከማሰብ የመነጨ ነው። የወጣቶች ህብረቱ እንቅስቃሴ የፖለቲካ ድጋፍን በማሰባሰብ እና የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲወጡ በማድረግ ረገድ ስትራጂካዊ ሚናውን ተጫውቷል። የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እ.አ.አ በ2006 ባደረገው ስብስባ የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት በድጋሚ የማደራጀት የውሳኔ ሀሳብ በማፅደቅ ህብረቱ የአህጉሪቷ የወጣት መዋቅር እንዲሆን በይኗል።
ሐተታዎች
የክህሎቶች ልማት፤ የአፍሪካ ቀጣይ የእድገት ምዕራፍ እና ግንባር
Oct 15, 2025 248
አፍሪካ የተስፋ እና የበረከት አህጉር ብቻ አይደለችም የዓለም ቀጣይ የእድገት ዳርቻ እና ማዕከል ጭምር እንጂ። ህዝቧ እ.አ.አ በ2024 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተሻግሯል፤ እ.አ.አ በ2050 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከአንድ ትውልድ በኋላ ባለንባት ምድር ላይ ከአራት ሰዎች መካከል አንዱ ከአፍሪካ እንደሚሆን ይጠበቃል። በጣም አስገራሚው ነገር ከ60 በመቶ በላይ አፍሪካውያን እድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች ሲሆን ይህም አፍሪካን ወጣቷ አህጉር አድርጓታል። ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ወጣት ትልቅ የስነ ህዝብ ትሩፋት ነው። ይህን አቅም ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ መጠቀም ከተቻለ አፍሪካን የዓለም ክህሎት መፍለቂያ፣ የፈጠራ እና ኢኖቬሽን ማዕከል ማድረግ ይቻላል።   ይሁንና የስነ ህዝብ ትሩፋት ብቻውን ልማት እንዲረጋገጥ አያስችልም። እውነተኛው ፈተና ያለው ይህን የተትረፈረፈ የሰው ሀብት በክህሎት የዳበረ፣ ለተለዋዋጭ ሁኔታዎች ራሱን ብቁ ያደረገ እና መፍጠር ወደ ሚችል የስራ ኃይል መቀየር ላይ ነው። የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 የሰው ኃይል “የምንፈልጋትን አፍሪካ ለመፍጠር” የሚያስችል ዋንኛ ምሰሶ እንደሆነ ያስቀምጣል። ይህ አህጉራዊ ማዕቀፍ በእውቀት እና ሁሉን አቀፍ እድገት አማካኝነት የበለጸገች፣ የተሳሰረች እና ራሷን የቻለች አህጉርን የመፍጠር ራዕይን አንግቧል። አፍሪካ የሰው ሀብት ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮ ሀብቶች ባለጸጋም ናት። አፍሪካ የዓለማችን 30 በመቶ የማዕድን ሀብት የሚገኝባት አህጉር ናት። ኮባልት፣ ሊቲየም፣ ፕላቲኒየም እና ሌሎች ውድ ማዕድናትን በስፋት ይገኙበታል። ማዕድናቱ አሁን ዓለም ላለችበት አረንጓዴ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሚባሉ ናቸው። የዓለማችን 60 በመቶ ያልታረሰ መሬት ያለው በዚችሁ አህጉር ነው። ይህ እርሻ የማያውቀው መሬት የዓለምን የምግብ ስርዓት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀየር አቅም አለው። ከ10 ቴራ ዋት በላይ የፀሐይ ኃይል የማመንጨት አቅም ያላት አፍሪካ ከአህጉር አልፋ የኢንዱስትሪ እና ዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በኃይል የማመንበሽበሽ አቅም አለው።   የኢኮኖሚ ማዕበሉም ወደ አፍሪካ ያደላ ይመስላል። እ.አ.አ 2021 ገቢራዊ መሆን የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና 55 ሀገራትን የሚያስተሳስር እና 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ተጠቃሚን በአንድ ማዕቀፍ ስር የሚያሳባስብ ነው። በአህጉር ደረጃ ዓመታዊ ጥቅል ምርቱ (ጂዲፒ) 3 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ይገመታል። አህጉራዊ የንግድ ማዕቀፉ በሙሉ አቅሙ ሲተገበር የአፍሪካ ሀገራትን የእርስ በእርስ የንግድ ልውውጥ መጠን 50 በመቶ እንደሚጨምረው የአፍሪካ ህብረት መረጃ ያመለክታል። ይህም ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማትን የሚያፋጥንና አህጉሪቷ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ልካ መልሳ ያለቀላቸውን ምርቶች በከፍተኛ ወጪ ከመግዛት ተላቃ ጥሬ ምርቶቿን በከፍተኛ ጥራት ወደ ማምረት ያሸጋግራታል። ይህ ትልቅ የኢኮኖሚ ትስስር እድል አፍሪካውያን በጋራ እንዲለሙ፣ የሙያ ክህሎት እንዲያሳድጉ እና የእውቀት ሽግግር እንዲያደርጉ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር ቀጣናዊ የእሴት ሰንሰለቶች እንዲፈጥሩ ያስችላቸዋል። እነዚህ ሁላ ተስፋ ሰጪ አቅሞች የሚቃረን አንድ የማይካድ ሐቅ አፍሪካ ውስጥ አለ ይህ እውነት የአፍሪካን የእድገት አቅም በሚፈለገው መልኩ የሚመግብ የክህሎቶች እና የስራ ክፍተት ነው። በየዓመቱ በአፍሪካ ከ10 እስከ 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ወጣቶች ወደ ስራ ይገባሉ። ይሁንና በአህጉሪቷ በዓመቱ የሚፈጠረው መደበኛ ስራ 3 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።   እንደ አፍሪካ ልማት ባንክ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ከሆነ ከአፍሪካ ወጣቶች መካከል አንድ ሶስተኛ ገደማው ስራ አጥ (Unemployment) ወይም ከአቅም በታች ሰራተኝነት (Underemployment) ውስጥ ነው። ይህ ስራ አለማግኘት ያለው በአፍሪካ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢነርጂ፣ ቴክኖሎጂ፣ በዲጂታላይዜሽን እና ሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች የሚገኙ ኩባንያዎች ክህሎት ያለው ሰው አጠረን እያሉበት ባሉበት ወቅት መሆኑ ትልቅ ጥያቄን ያስነሳል። በትምህርት ስርዓቱ እና በገበያው ፍላጎት መካከል እንዴት እንደዚህ አይነት አለመጣጣም ሊመጣ ቻለ? የሚል። በትምህርት እና በኢንዱስትሪው መካከል ባለው ያለመተሳሰር ችግር ምክንያት አፍሪካ በየዓመቱ 130 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ምርታማነት (productivity) ታጣላች። እዚህ ጋር መነሳት ያለበት ጉዳይ ፈተናው የአቅም ሳይሆን ትምህርት እና ስራን፣ ፖሊሲ እና ተግባርን እና ስልጠናን ከቴክኖሎጂ ጋር የሚያስተሳሰር መስመር አለመዘርጋቱ ነው። በአፍሪካ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከላት እየሰሩ ያሉት ከኢንዱስትሪው ርቀው ነው ማለት ይቻላል ይህም ተመራቂዎች የስራ ገበያው የሚፈልገውን ክህሎት እና አቅም እንዳይታጠቁ አድርጓል። ሌላኛው ፈተና በአፍሪካ የተንሰራፋው ኢ-መደበኛ ኢኮኖሚ ነው። አንዳንድ ጥናቶች የአፍሪካን ኢ-መደበኛ የኢኮኖሚ ድርሻ እስከ 85 በመቶ ያደርሱታል። ይህም ዜጎች ክህሎታቸውን እንዳያሳድጉ እና የብቃት ማረጋገጫን እንዳያገኙ እክል ፈጥሯል። የአፍሪካን ክህሎት ምህዳር በመቀየር የኢንዱስትሪ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ፣ የስራ እድል ፈጠራን ማሳደግ እና ዘላቂ ልማትን ማረጋገጥ ላይ የጋራ ትብብርን ማጠናከር አበይት ትኩረቱ ያደረገ ሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።   “አፍሪካውያንን የአፍሪካ የኢንዱስትሪ ልማት የሚያፋጥኑበትን ክህሎቶች ማስታጠቅ” የሳምንቱ መሪ ሀሳብ ነው። ሁነቱን ያዘጋጁት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ነው። በሁነቱ መክፈቻ ላይ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ እና የህብረቱ ከፍተኛ አመራሮች እና የአባል ሀገራት ሚኒስትሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎች፣ የልማት ተቋማት አመራሮች፣ መምህራን፣ ኢኖቬተሮች፣ የወጣት ተወካዮች እና የልማት አጋሮች ተሳትፈውበታል። የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክህሎቶች ለሀገራዊ ግቦችና ለአህጉራዊ የ2063 የልማት አጀንዳዎች መሳካት ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ናቸው።   ኢትዮጵያ ለክህሎት ልማት በሰጠችው ትኩረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው ብለዋል። ክህሎት መር የፖሊሲ እርምጃችን ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ የስራ ፈጣሪነት ባህልን በንቃት እያስተዋወቀ መሆኑን ተናግረዋል። ተመራቂዎች የራሳቸውን ስራ እንዲጀምሩ እና እድገት እንዲያመጡ የሚያስፈልጋቸውን ስልጠና፣ ምክር እና የገንዘብ ድጋፍ እያመቻቸ መሆኑን አመላክተዋል። በስልጠና ተቋማት እና በኢንዱስትሪዎች መካከል ያለውን ትብብር የማጠናከር ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በበኩላቸው የህዝባችንን አቅም ወደ ውጤታማ፣ አሳታፊ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ወደሆነ የሥራ ኃይል መለወጥ አለብን ብለዋል።   ክህሎት የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ማዕከል መሆኑን ተናግረዋል። የክህሎት ልማት ለአሳታፊ ዕድገትና ለተገቢ የሥራ ዕድሎች ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የትግበራ ዕቅድ አካል መሆኑን ጠቁመዋል። አባል ሀገራት ሀገራዊ ለውጦችን ከአህጉራዊ ፍላጎቶች ጋር ለማጣጣም በጋራ መስራት እንዳለባቸውም አስገንዝበዋል። የተሻለ፣ ፈጣን እና ይበልጥ አሳታፊ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ያለውን የለውጥ አቅም መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል። የፖሊሲ ወጥነትን እና ቀጠናዊ ትብብርን ማጠናከር እንደሚገባ ጠቁመዋል። የአፍሪካ ክህሎት ክፍተትን መሙላት፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ለክህሎት ልማት መጠቀም እና በአጀንዳ 2063 አማካኝነት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ ላይ ውይይት ይደረጋል። በሳምንቱ የሚኒስትሮች እና የግሉ ዘርፍ የምክክር መድረኮች፣ የክህሎት አውደ ርዕዮች እና የገበያ ትስስር ሁነቶች እንዲሁም የወጣቶች እና የስራ ፈጣሪዎች ፎረም እንደሚካሄድ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ፎረሙ የአፍሪካ ኢኖቬተሮች የስራ ውጤቶች ይቀርቡበታል። የክህሎቶች ሳምንት ተሳታፊዎቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እና በኢኖሼሽን ማዕከላት ውስጥ ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የሰው ኃይል ልማት ስራዎች ይጎበኛሉ። ሳምንቱ እስከ ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የአፍሪካ ክህሎት ልማት አስመልክቶ የጋራ አቋም መገለጫ እና የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።   የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ለአህጉሪቷ የኢንዱስትሪ እና ክህሎት አጀንዳ ተጨባጭ አሻራ የሚያሳርፍ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል። የመጀመሪያው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት እ.አ.አ ኦክቶበር 2024 በጋና አክራ መካሄዱ የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ክህሎቶች ፈተናዎች ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኝ እንዲሁም ምህዳሩን ለመቀየር አህጉሪቷ በዘርፉ አብዮት ያስፈልጋታል ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህን የስነ ህዝብ ትሩፋት ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን ክህሎት እና የሰለጠነ የሰው ኃይል መቀየር ይገባል። ይህን ለማድረግ የተቀናጀ እና አህጉር አቀፍ ጥረት ያስፈልጋል። የሁለተኛው የአፍሪካ ክህሎቶች ሳምንት ስኬት የሚለካው በንግግሮች እና በጋራ መግለጫዎች ሳይሆን ራዕዮቹን በአፍሪካ ትምህርት ተቋማት፣ ስልጠና ማዕከላት እና ኢንዱስትሪዎች በተጨባጭ በመቀየር እና ውጤት በማምጣት ነው። በዚህ ረገድም መንግስታት፣ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የአፍሪካን የክህሎት ልማት መጻኢ ጊዜ በውድድር፣ በፈጠራ እና አሳታፊነትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊገነቡ ይገባል። አፍሪካ ወጣቶቿ በክህሎት እና በእውቀት ከታጠቁ አፍሪካ የተለመቻቸውን ግዙፍ እቅዶች እና ትላልቅ ውጥኖች ባጠረ ጊዜ እንዲሳኩ ያስችላል።
 ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ በሀገሩ ህልሙን እውን ያደረገው ወጣት...
Oct 9, 2025 413
ሐረር ፤መስከረም 29/2018 (ኢዜአ)፦በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ነስረዲን አህመድ፤ በውጭ ሀገር ሰርቶ መለወጥን በማሰብ ከአመታት በፊት ወደ አረብ ሀገር ለመሄድ እንቅስቃሴ ጀመረ። የመጓዝ እቅዱም ተሳካለትና በዱባይ ለስምንት ዓመታት በስራ ላይ ማሳለፉን ያስታውሳል፤ በበረሃው ምድር ሌት ተቀን በስራ እየደከመ ህይወቱን ሊለውጥለት የሚችል ገንዘብ ለመያዝ ቢጥርም ባሰበው ልክ ሊሳካለት አልቻለም።   በመሆኑም ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገሩ በመመለስ ሰርቶ የመለወጥ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ሳይውል ሳያድር ወደ ስራ ገባ። ከበረሃው ንዳድ ወጥቶ በሀገሩ ሰርቶና አልምቶ መለወጥን የሰነቀው ነስረዲን በሀረር የንብ ማነብ ስራን ከጀመረ ሶስት ዓመታት እንደሆነው ያስታውሳል። በምንሰራበት የስራ መስክ ሁሉ በትጋት ሌት ከቀን መስራት ከቻልን የማናሳካው ነገር አይኖርም የሚለው ወጣቱ አሁን በሀገሩና በወንዙ በስኬት መንገድ ላይ መሆኑን ይናገራል።   የነስረዲን የንብ ማነብ ስራ የተጀመረው በጥቂት ቀፎዎች የነበረ ቢሆንም በስድስት ወራት ውስጥ ግን 50 ቀፎዎች ማድረስ መቻሉን ያስታውሳል። በሀገሬ ህልሜ እውን እየሆነ ነው የሚለው ወጣቱ የንብ ማነብ ስራውን አጠናክሮ በመቀጠል አሁን ላይ የንብ ቀፎዎቹን 300 ሲያደርስ ለ30 የአካባቢው ወጣቶችም የስራ እድል ፈጥሯል። በአረብ ሀገር የቆየባቸውን ዓመታት በቁጭት የሚያስታውሰው ነስረዲን መልፋትና መድከም ከተቻለ በሀገር ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል እኔ ጥሩ ማሳያ ነኝ ይላል። ከአረብ ሀገር የአመታት እንግልት በኋላ ወደ ሀገሬ ተመልሼ የስኬት መንገድን ጀምሬያለሁ በቀጣይም ጠንክሬ እሰራለሁ ብሏል።   በቀጣይ ከንብ ማነብም ባለፈ የማር ማቀነባበርያ አነስተኛ ኢንዱስትሪ የማቋቋም ትልም እንዳለው ተናግሮ ለዚህም እንደሚተጋ አረጋግጧል። በዚሁ የልማት ፕሮጀክት ላይ የስራ እድል የተፈጠረለት ወጣት ሸዊብ መሀመድ፤ ከዚህ ቀደም ያለምንም ስራ ተቀምጦ መሽቶ ይነጋ እንደነበር አስታውሶ አሁን እያገኘ ባለው ገቢ ከራሱ አልፎ ቤተሰብ እየረዳ መሆኑን ተናግሯል።   ወጣት በድሪ ሙሳም፤ በነስረዲን ጥረት እርሱን ጨምሮ ብዙ ወጣቶች ስራ የተፈጠረላቸው በመሆኑ ጥሩ ገቢ እያገኙ መሆኑን አንስቶ በቀጣይ እርሱም የራሱን ተመሳሳይ ስራ ለመጀመር ማቀዱን ገልጿል።   በሐረሪ ክልል ግብርና ልማት ቢሮ የንብ እርባታ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢብሳ ዩስፍ፤ የነስረዲን ጥረትና የአጭር ጊዜ ስኬት ለሌሎች ወጣቶችም ጥሩ ተሞክሮ የሚሆን ነው ብለዋል።   በመሆኑም በክልሉ የማር ምርታማነትን ለማጎልበት በከተማና በገጠር ወረዳዎች ላይ የንብ መንደር በመመስረት ዘርፉን የማጎልበት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአፍሪካ መምህራን፤ የአህጉሪቷ መጻኢ ጊዜ ቀራጺዎች
Oct 3, 2025 613
አፍሪካ በወጣቶች የታደለች ሀገር ናት። ከአህጉሪቷ ህዝብ መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው እድሜው ከ25 ዓመት በታች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜን የሚወስነውን ወጣት ማን ያስተምረዋል? የሚለው ጥያቄ ቁልፍ ነው። ይህ ጥያቄ ከመማሪያ ክፍሎች እና መጻሕፍት ባለፈ የአፍሪካ ልማት አበይት አጀንዳ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። በዓለም ደረጃ ትልቅ የእድገት እና የልማት ሞተር የሆነውን ወጣት በብዛት የያዘችው አፍሪካ ትውልዱን የሚቀርጽ መምህራን ውጪ ህልሟን ማሳካት የሚታሰብ አይሆንም። የአፍሪካ ህብረት በአህጉር አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እ.አ.አ በ2030 በትንሹ 15 ሚሊዮን አዲስ መምህራን እንደሚያስፈልጉ አስታውቋል። ይህን ግብ ለማሳካት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እና ጠንካራ ሪፎርሞችን ማድረግ ይጠይቃል። አፍሪካ የትምህርት መሰረተ ልማትን ለማሻሻል፣ የመምህራንን ቁጥር ለመጨመር እና በትምህርት ዘርፍ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት 90 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ሲል ህብረቱ ገልጿል። ጉዳዩ ከትምህርት ባለፈ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ አንድምታ ያለው ነው። መምህራን የእያንዳንዱ ክህሎት፣ ስራ እና ኢኖቬሽን የሀሳብ መሐንዲስ ናቸው። የአፍሪካ መጻኢ ጊዜ የመወሰን አቅም አላቸው። በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የመምህራን ትምህርት ስርዓታቸው ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ይገኛል። የአፍሪካ መዲና የሆነችው ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ በርካታ ሪፎርሞችን እያደረገች ሲሆን ከዚህ ውስጥ አንዱ የመምህራንን አቅም መገንባት እና የብቃት ደረጃን ማሳደግ ይገኝበታል። የትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሄራዊ የመምህራን ልማት ንቅናቄ በማድረግ መምህራን በተለያዩ የትምህርት እርከኖች አቅማቸውን እንዲጎለብት ተከታታይ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራም አማካኝነንት ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራን የዲጂታል ክህሎታቸው በማዳበር እና ተከታታይ የብቃት ምዘና በማድረግ አቅማቸውን እየተገነባ ይገኛል። በነዚህ ስራዎች የትምህርት ውጤት ላይ አበረታች መሻሻሎች ታይተዋል። መንግስት የሰለጠነ መምህራንን ቁጥር ማሳደግን የሪፎርሙ አካል አድርጎ እየሰራ ነው። ጋና የመምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ወደ ዩኒቨርስቲ በማሳደግ ሙያዊ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኬንያ ብቃት ላይ የተመሰረተ የስርዓተ ትምህርት ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የመምህራን መማር ማስተማር የበለጠ ተግባር ተኮር እና ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን የጀመረችው ተግባር ተጠቃሽ ነው። ሩዋንዳ የስርዓተ ትምህርት አሰራሮቿን ከመምህራን ስልጠና ጋር በማጎዳኘት የመምህራን እጥረትን ለመቀነስ እና ክህሎታቸውን ለማሳደግ እየሰራች ነው። ለትምህርት ዘርፍ የሚመደበው በጀት በቂ አለመሆን፣ የተማሪ እና ክፍል ጥምርታ አለመመጣጠን፣ የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትስስር በሚፈለገው ደረጃ አለማደግ፣ የዲጂታል ክህሎት ማነስ እና ከፍላጎት አንጻር በቂ የሰለጠነ መምህራን አለመኖር የአህጉሪቷ የትምህርት ዘርፍ ፈተናዎች ናቸው። የፓን አፍሪካ የመምህራን ትምህርት ኮንፍረንስ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ተካሄዷል። "በአፍሪካ የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር” በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው ኮንፍረንስ የትምህርት ሚኒስትሮች፣ የመምህራን ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራን፣ የግሉ ዘርፍና የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ለሰው ሃብት ልማትና ለምጣኔ ሀብት ቁልፍ ሚና አለው ብለዋል። በአፍሪካ የሚፈለገውን ልማትና ዕድገት ለማምጣት የትምህርት ተደራሽነት ላይ መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፎርሞችን ተግባራዊ ማድረጓንና በዚህም ውጤት መገኘቱን አንስተዋል። የመምህራንን አቅም ለመገንባት የተለያዩ ስልጠናዎች በመስጠት በኩልም የተሻለ ስራ መሰራቱን ነው ሚኒስትር ዴኤታዋ የጠቀሱት። የትምህርት ጥራትና የመምህራን እጥረት ላይ እንደ አህጉር አሁንም ያልተፈታ ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አባል ሀገራቱ ትብብራቸውን የበለጠ ማጠናከር አለባቸው ብለዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነር ፕሮፌሰር ጋስፓርድ ባንያንኪምቦና በበኩላቸው በአፍሪካ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባትና ሳይንስና ፈጠራን የበለጠ ለማዳበር የመምህራንን አቅም ማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል። ለዚህም ለመምህራን አቅም ግንባታ የተለያዩ ኤኒሼቲቮች ተቀርጸው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ የአፍሪካ የ2063 የልማት ዕቅዶች ዕውቀት መር በሆነ መንገድ ቢተገበሩ ውጤታማ ይሆናሉ ብለዋል። የአፍሪካ መምህራንን አለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፈጣንና ተለዋዋጭ ቴክኖሎጂ ጋር መላመድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። በአፍሪካ የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን የበለጠ ለማሳደግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ከወቅቱ ጋር ማዛመድ ይገባል ብለዋል። በኮንፍረንሱ ላይ መምህራንንና ትምህርትን የተመለከቱ የተለያዩ አህጉራዊ ስትራቴጂዎች ይፋ ተደርገዋል። የአፍሪካ የትምህርት ስትራቴጂ (ከእ.አ.አ 2026 እስከ 2035 የሚተገበር) የአፍሪካ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስትራቴጂ፣ የአፍሪካ ሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ስትራቴጂ እንዲሁም የአፍሪካ የትምህርት የክህሎት ልማት የድርጊት መርሃ ግብር ይፋ ሆነዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ መምህራትን ማህበረሰብ የአሰራር ማዕቀፍ ወደ ትግበራ ገብቷል። ይፋ የሆኑት ስትራቴጂዎች እና የአሰራር ማዕቀፎች የመምህራን ትምህርት፣ ሙያዊ ልህቀት፣ መሰረተ ትምህርት፣ ዲጂታል ክህሎቶች እና ኢኖቬሽን ተኮር የማስተማር ዘዴ ላይ መዋቅራዊ ለውጦችን የማምጣት ግብ እንዳላቸው የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል። በኮንፍረንሱ ላይ የ2025 የአፍሪካ መምህራን ሽልማት የተካሄደ ሲሆን የዘንድሮው የዓለም የመምህራን ቀን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። አህጉራዊው ሁነት በአፍሪካ የመምህራን ድምጽ የበለጠ ጎልቶ እንዲሰማ የማድረግ ፣ የትምህርት ኢንቨስትመንት መጠን እንዲያድግ እና የባለድርሻ አካላት ትብብርን የማጠናከር አላማ እንዳለው ተገልጿል። የመምህራንን አቅም ማሳደግ የአፍሪካ የትምህርት ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ አበይት ትኩረቶች መካከል አንደኛው መሆኑን ህብረቱ በመረጃው አመልክቷል። ህብረቱ እ.አ.አ 2024 የትምህርት ዓመት ብሎ በመሰየም የሰጠው ስትራቴጂካዊ ትኩረት የዚሁ ማሳያ ነው። የፓን አፍሪካ ኮንፍረንሱ የመምህራን ትምህርት የአፍሪካ የልማት አጀንዳ አበይት ትኩረት መሆኑ በግልጽ ታይቶበታል። የመምህራንን እጥረትን መቀነስ ብዙ መምህራንን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን ስልጠና ጥራት ያለው፣ ነባራዊ እውነታን ያገነዘበ እና መጻኢውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የአፍሪካ መንግስታት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ አጋሮች የመምህራን ትምህርት ስርዓትን መቀየር ትኩረታቸውን ባደረጉበት በአሁኑ ወቅት የአፍሪካን መጻኢ ጊዜ የቀና የሚያደርገውን አፍሪካዊ ማን ያስተምራል? የሚለው ጥያቄ ተስፋ የሚሰጥ ምላሽ ያገኛል። የሰለጠነ፣ በክህሎት የዳበረ እና የኢኖሼሽን እውቀቱ ያደገ መምህር ለአፍሪካ ቀጣይ ጉዞ መቀናት ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል።  
  "ያሆዴ"- ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት
Sep 28, 2025 700
(በማሙሽ ጋረደው - ከኢዜአ ሆሳዕና ቅርንጫፍ) የሀዲያ የአዲስ ዘመን መለወጫ በዓል የሆነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው። ለማህበራዊ የህይወት አመራር ጉልህ አስተዋጾም ስላለውም በሀዲያዎች ዘንድ በየዓመቱ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበራል፡፡ "ያሆዴ" ያለፈውን አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲስ ዘመን የሚቀበሉበት፤ የመጻኢ ተስፋ ብስራትና የልምላሜ ምልክትም ጭምር ተደርጎም ይቆጠራል፡፡ በመሆኑም በዓሉ ሲቀርብ የሀዲያ ተወላጆችና የበዓሉ ተሳታፊዎች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ከያሉበት ወደአካባቢው በመምጣት ይሰባሰባሉ፡፡ በዘንድሮ የያሆዴ በዓልም የሀድያ ተወላጆች የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ በተዘጋጀ ስፍራ (ነፈራ) ተሰባስበው በዓሉን በድምቀት አክብረውታል፡፡ በበዓሉ አከባበር ያለፈው ዓመት ስኬትም ይገመገማል፤ በአዲሱ ዓመትም የተሻለ ተሰርቶ ስኬት እንዲመዘገብ በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት ይካሄዳል። ሊተገበር የሚችል ዕቅድም ይታቀዳል፡፡ በግልና በቤተሰብ የመጡ ስኬቶች በጋራ በመሆን ይገመገማሉ። የበረቱና ውጤት ያስመዘገቡም እንዲበረታቱ ይደረጋል። ለዚህም ነው "ያሆዴ" የማህበራዊ መስተጋብር መሰረት ነው የሚባለው። ሰዎች እንዲሰሩና ስኬት እንዲያስመዘግቡ የሚያበረታታ እሴት አለው። የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፋን ቦጋለ እንደሚሉት የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል "ያሆዴ" ከተናጠል ይልቅ በትብብር የመድመቅ ተምሳሌት ነው፡፡ ከነሐሴ ወር አጋማሽ ጀምሮ የበዓሉ መቃረብን የሚያበስሩት ታዳጊ ልጆች ናቸው። ልጆቹ የዋሽንት (ገምባቡያ) ድምጽ ማሰማት ከጀመሩ በጉጉት የሚጠበቀውን የዘመን መለወጫ "ያሆዴ" በዓል መድረሱ ምልክት ነው። በዓሉ ሀድያዎች አሮጌውን ዓመት ሸኝተው አዲሱን ዓመት የሚጀምሩበት ወቅት ነው። በዓሉ የብሩህ ተስፋ፣ የሠላም፣ የፍቅር፣ የረድኤት፣ የበረከት ተምሳሌት በመሆኑም የተለየ ትርጉምና ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ በዓሉ ሲከበር በተለያዩ ምክንያቶች ተራርቀው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት ከያሉበት ይሰባሰባሉ። በዓሉ በአማረ መልኩ እንዲከበርም ሁሉም የቤተሰብ አባላት የየራሳቸው የሥራ ድርሻቸውን ያከናውናሉ።   አባውራዎች ለበዓሉ ሠንጋ መግዣ የሚሆን ገንዘብ በቱታ ወይም በቅርጫ ቡድናቸው አማካኝነት እየቆጠቡ ይቆያሉ። እንዲሁም ለእንስሳት የሚሆን የግጦሽ ሳር የሚያበቅል ቦታ ከልለው ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሚሆነበት ምክንያት ደግሞ በዓሉ በሚከበርበት ሰሞን የሰው ልጅ ይቅርና እንስሳትም መጥገብ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ነው፡፡ እማውራዎች ከበዓሉ ሦስትና አራት ወራት አስቀድመው እንሰት በመፋቅ ቆጮና ቡላ ያዘጋጃሉ። በተጨማሪም ከአካባቢው እናቶች በጋራ በመሆን (ዊጆ) የተሰኘ የቅቤ እቁብ በመግባት ለበዓሉ የሚሆን ቅቤ ማጠራቀም ይጀምራሉ፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ ለአተካናና ለሥጋ መብያ ናቀሮ ወይም ዳጣን እንዲሁም የሚጠጣ ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ የማዘጋጀት ድርሻ የእናቶች ነው፡፡ ለበዓሉ የቤት ውስጥና የውጭ ግርግዳን በቀለምና በተለያዩ ጌጣጌጦች የማስዋብ ሃላፊነት ደግሞ የልጃገረዶች ነው። ወጣት ወንዶች ከነሀሴ መግቢያ ጀምሮ አባቶቻቸው የሚያሳዩዋቸውን ግንድ በመቁረጥ ለምግብ ማብስያ እንዲውል ፈልጠው ያዘጋጃሉ። በሀዲያዎች አጠራር ለችቦ የሚሆን እንጨት ወይም ጦምቦራ ከጫካ ለቅመው አስረው እንዲደርቅም ያስቀምጣሉ፡፡ ለበዓሉ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት የሚያደርገው ጥረት በዓሉ በስኬትና በድምቀት እንዲከበር ጠቀሜታው የጎላ ነው። በዚህም ያሆዴ ከተናጠል ይልቅ ትብብርን የሚያጠናክር ነው ማለት ይቻላል። እሴቱ በትብብር መድመቅ እንደሚቻልም የሚያሳይ ነው።   ይህን ሀሳብ የሚጋሩት አቶ መስፍን የሀዲያ የዘመን መለወጫ በዓል በምንም ሁኔታ መነጣጠል የማይቻል ትስስርን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን ይገልጻሉ። ሀገራዊ አንድነትና አብሮነትን የሚያጠናክር ዘመናትን የተሻገረና ከፍተኛ ተቀባይነት ያለው ባህላዊ እሴት ያለው መሆኑንም ይናገራሉ። በዓሉ ሊከበር ጥቂት ቀናት ሲቀረው አባውራዎች በቅርጫ ማህበራቸው አማካኝነት ያጠራቀሙትን ገንዘብ በመያዝ የእርድ በሬ ይገዛሉ። በዚህ ወቅት ገንዘብ ማዋጣት ያልቻሉ የቅርጫ አባላት እህል በሚደርስበት ወቅት ለመክፈል ተስማምተው በሬውን በዱቤ እንዲገዙ ይደረጋል፡፡ ይሄም የሚሆነው በያሆዴ በዓል አንዱ ሲበላ ሌላው ተመልካች መሆን ስለሌለበት ነው። እርስ በርስ መጨካከን እንዳይኖርና በዓሉን በአብሮነት ሁሉም ተደስቶ ማክበር እንዲችል ለማድረግ ነው። ከበዓሉ ዕለት በፊት ያለው የመጨረሻ ገበያም የእብድ ገበያ (መቻዕል ሜራ) የሚል ስያሜ አለው። ይሄ ሥያሜ ያገኘው በዓሉ ሲቃረብ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ውጥረት ታሳቢ በማድርግ ነው፡፡ በዚህ የእብድ ገበያ ህብረተሰቡ መገበያየት የሚጀምረው ጠዋት ማለዳ ጀምር ሲሆን የግብይት ሂደቱ የሚጠናቀቀው ደግሞ እኩለ ቀን ላይ ነው፡፡ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለመግዛትና የያሆዴ በዓል ከተከበረ በኋላ ለአንድ ወር ገበያ ስለማይቆም ይህን ታሳቢ ያደረገ ግብይት ለመፈጸም የግብይት ሂደቱ ጥድፊያ የበዛበት ሆኖ ይታያል።   ያሆዴ በዓል መከበር የሚጀምረው በአተካን ሂሞ ወይም በአተካና ምሽት ሲሆን ይህም ከበዓሉ አንድ ቀን በፊት ያለው ምሽት ነው። ስያሜውን ያገኘው "አተካና" ከተሰኘና በያሆዴዎች ዘንድ ለክብር እንግዳ እና በዘመን መለወጫ ከሚዘጋጅ ምግብ ነው። አተካና ከወተት፣ ከአይብ፣ ከቡላ፣ ከቅቤና ከሌሎች የቅመማ ቅመም ውጤቶች የሚዘጋጅ ምግብ ሲሆን በጣም ጣፋጭና የምግበ ፍላጎትን የሚጨምር ምግብ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ይሄንን የተለየ ምግብ ተሰባስቦ በአብሮነት በመመገብ በደመቀ መልኩ በዓሉን ማክበር ይጀምራል፡፡ የአካባቢው አባቶች በወጣቶች የተዘጋጀ የማቀጣጠያ እንጨት (ሳቴ) ይዘው ትልቅ በሚባሉ አባውራ ቤት ደጃፍ ወደ ተዘጋጀው የችቦ ደመራ (ጦምቦራ) ቦታ ይመጣሉ:: የሀገር ሽማግሌች አዲሱ ዓመት የብርሃን ዓመት እንዲሆን፤ ለሀገርና ለህዝቦቿ ሰላም እንዲጸና፤ አብሮነት እንዲጠናከር፣ ሰላምና ፍቅር እንዲነግስ ፈጣሪያቸውን ከተማጸኑ በኋላ ችቦውን በእሳት ይለኩሳሉ፡፡   ችቦው ከተለኮሰ በኋላ የአካባቢው ወጣቶች ተሰባስበው ያሆዴ …ያሆዴ! …ያሆዴ! በማለት እየጨፈሩ ያነጋሉ ይጨፍራሉ:: በሀድያዎች ዘንድ "ያሆ" ማለት የአዲስ ዓመት መግባትን ተከትሎ ማብሰሪያ ጭፈራ ሲሆን "ኤዴ" ማለት ደግሞ አገናኝ ማለት ነው፡፡ በያሆዴ በዓል የእርድ ሥነ ስርዓት ለማከናወን ነዋሪዎች የሚሰበሰቡበት ስፍራ "ነፈራ" የሚል ስያሜ አለው። የተለያዩ ማህራዊና ባህላዊ ክዋኔዎችን ለመከወን እንዲመች ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሰፋ ያለ ቦታ ሰሆን በተለያዩ የጥላ ዛፎች የተዋበና ለዚሁ ተግባር የተዘጋጀም ነው። በእለቱ ለእርድ የተዘጋጀው ሠንጋ ከቀረበ በኋላ የባህል ሽማግሌዎች የበሬውን ሻኛ በሰርዶ ሳር ለጋ ቅቤ ይቀባሉ፤ ወተትም ያፋሱበታል፡፡ ይህ ባህላዊ ሥነ ስርዓት ጋቢማ የሚባል ሲሆን (የመልካም ምኞት) መግለጫ ስነ ስርዓትም ነው፡፡ ይህም ሥነስርአት በሚከናወንበት ወቅትም "ክፉ ቀን አይምጣ፣ ርሃብ ሰቀቀን ይጥፋ፣ ጥጋብ ይስፈን፣ በአካባቢው በሀገሩ ጥጃ ይቦርቅ፣ ልጅ ይፈንጭበት፣ አገር ሰላም፣ ገበያ ጥጋብ ይሁን፣ ሰማይና ምድሩ ይታረቁን " እያሉ በአባቶች ምርቃት ከተካሄደ በኋላ የእርድ ስነ ስርዓት ይከናወናል፡፡ የእርድ ሥነ ስርዓቱ የተከናወነበት ቤት እማወራ አስቀድመው ባደረጉት ዝግጅት መሰረት ቅቤ፤ (ቦርዴ፣ ቃሪቦ፣ ጠጅ፣ ብርዝ) እንዲሁም ከታረደው የበሬ ሥጋ አርዚ ማራ (ቅምሻ) ይወሰድና ክትፎ ከተዘጋጀ በኋላ በጋራ እየበሉ እየተጫወቱ ይውላሉ፡፡ በዚህም በቅርጫ ሥጋው ላይ ከሚሳተፉት የቤተሰብ አባላት ውጪ በአካባቢው የሚገኙ አቅመ ደካሞችም ጭምር አብረው በመብላት በመጠጣት በዓሉን በአንድነት ያሳልፋሉ፡፡ ቀሪውን የቅርጫ ሥጋም አባላቱ ተከፋፍለው ወደ እየቤታቸው ይወስዱታል፡፡ በዓሉ አብሮ የመብላት፣ የመጠጣት፣ የመጠያየቅ፣ ችግርንና ግጭትን በጋራ ተወያይቶ የመፍታት፣ መፈቃቀርና መተሳሰብን የሚፈጥር፣ አቅመ ደካሞችና የተቸገሩ የሚረዱበት የአብሮነት መገለጫ በመሆኑ በተለየ መልኩ ይከበራል፡ ከእርድ ሥርዓቱ በኋላ በማግስቱ ልጆች አደይ አበባ (ዘራሮ) ይዘው ወደ ወላጆቻቸው እየጨፈሩ ይመጣሉ። የመስቀል አበባ እንደሚኖር ኑሩ ይባላሉ። ከስጋውም፣ ከቦርዴውም፣ ከአተካናውም እንዲመገቡ ያደረጋል። ይህ ስነ ስርዓትም ሚክራ ይባላል። በያሆዴ የዘመን መለወጫ በዓል ትዳር የያዙ ሴት ልጆችም ከባሎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ወላጆቻቸው ምግብ ሰርተው፣ የሹልዳ ሥጋና አደይ አበባ ጭምር ይዘው ይሄዳሉ። በዓሉ ያላገቡ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ለአዲስ ህይወት ጅማሬ የሚያበስሩበት በመሆኑን የተለየ ድባብ አለው፡፡ የያሆዴ በዓል ካሉት እሴቶች አንዱ የህብረተሰቡን የአካባቢ ልማት ተሳትፎ ማበረታታት ተጠቃሽ መሆኑን የገለጹት አቶ መስፍን ዕሴቱ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናቅቀው ለማህበረሰብ ጥቅም እንዲውሉ ጭምር አቅም እየሆነ መምጣቱን ነው የሚናገሩት።ይህ የአብሮነት ማስተሳሰሪያና የማህበራዊ መስተጋብር መጋመጃ የሆነው በዓል እሴቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል መስራት ይገባል። እሳቸው እንዳሉት በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዩኔስኮ ወካይ ቅርስነት እንዲመዘገብ ለማስቻል እየተሰራ ነው፡፡ ለዚህም መምሪያው ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ዕሴቱን የመሰነድና ምርምሮች ማካሄድን ጨምሮ እያከናወናቸው ያሉ የተለያዩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው።  
ትንታኔዎች
ማድያት እና ህክምናው
Sep 29, 2025 996
ማድያትን ለማከም አስቸጋሪ መሆኑንና በታካሚዎች ላይም የሥነ ልቡና እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያመጣ የሚችል መሆኑን የቆዳ ሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ስለ ማድያት መንስዔ፣ ስለሚከሰትበት የሰውነት ክፍል፣ ማድያት ያለበት ሰው ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ፣ ቆዳን ስለሚያስቆጣ ሠርካዊ ልማድ እና ሕክምናውን በተመለከተ በራስ ደስታ ዳምጠው መታሰቢያ ሆስፒታል የቆዳ እና አባላዘር በሽታዎች ስፔሻሊስት ዶክተር አደራጀው ብርሃን ከኢዜአ ቆይታ አድርገዋል። በማብራሪያቸውም፤ በቆዳ ውስጥ ያሉ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) ከመጠን በላይ ቀለም ሲያመርቱ ማድያት ተከሰተ እንደሚባል ገልጸዋል። ለዚህም መንስዔው የተፈጥሮ ተጋላጭነት ከተለያዩ ቀስቃሽ ምክንያቶች ጋር የሚያደርጉት መሥተጋብር መሆኑን አስረድተዋል። 👉 የማድያት መንስዔ ምንድን ነው? 1ኛ. የሆርሞን ለውጥ፡- በእርግዝና ወቅት ወይም የወሊድ መቆጣጠሪያ ሲጠቀሙ የሚኖር የሆርሞን ለውጥ ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ያደርጋል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። 2ኛ. የፀሐይ ጨረር፡- ከልክ ያለፈ ፀሐይ ቀለም አምራች ኅዋሶች(ሴሎች) በብዛት ቀለም እንዲያመርቱ ስለሚያነቃቃ፤ የፀሐይ ጨረር ዋነኛ ቀስቃሽ እና አባባሽ ምክንያት መሆኑንም ገልጸዋል። 3ኛ. የዘር ሐረግ፡- በቤተሰብ ውስጥ ማድያት ካለ በዘር የመተላለፍ ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ይናገራሉ። 4ኛ. የቆዳ ዓይነት፡- ጥቁሮች (ከቡናማ እስከ ጥቁር የቆዳ ቀለም ያላቸው) ንቁ ቀለም አምራች ሴሎች ስላሏቸው ለማድያት የሚኖራቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑን ነው የተናገሩት። 5ኛ. ሌሎች መንስዔዎች፡- ሙቀት (የሚታዩ እና የማይታዩ ጨረሮች እንዲሁም የምድጃ እሳት)፤ የተለያዩ መድኃኒቶችና የመዋቢያ ምርቶች፤ የእንቅርት ዕጢ ህመሞች እንዲሁም ጭንቀት ማድያት እንዲከሰት ወይም እንዲባባስ ከሚያደርጉ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውንም የሕክምና ባለሙያው አስገንዝበዋል። 👉 ማድያት በየትኛው የቆዳ ክፍል ላይ ይከሰታል? ማድያት ከሚከሰትበት የቆዳ እና የሰውነት ክፍሎች አንጻር በሁለት ከፍሎ ማየት እንደሚቻል ዶክተር አደራጀው አንስተዋል። እነሱም 1ኛ. ከሚከሰትበት የቆዳ ክፍል አንጻር፡- ማድያት በውስጠኛውም ሆነ በላይኛው የቆዳ ክፍሎች ላይ ወይም በሁለቱም ላይ ሊከሰት ይችላል ብለዋል። 2ኛ. ከሚከሰትበት የሰውነት ክፍሎች አንጻር፡- የሕክምና ባለሙያው እንዳሉት 60 በመቶ ማድያት ግንባር፣ ጉንጭ፣ አፍንጫ፣ የላይኛው ከንፈር እና አገጭ ላይ ይከሰታል ብለዋል። 30 በመቶው ደግሞ ጉንጭ እና አፍንጫ ላይ እንዲሁም 10 በመቶው የአገጭ መስመርን ተከትሎ እንደሚከሰት አስረድተዋል። በሌላ በኩል አልፎ አልፎ ከፊት የሰውነት ክፍሎች በተጨማሪ በደረት፣ አንገት እና ክንድ ላይ የሚከሰትበት ሁኔታ መኖሩንም ጠቁመዋል። 👉 የማድያት ባሕርይ ማድያት የቆዳ ቀለም ለውጥ ያመጣል፤ በግራና በቀኝ የፊት ክፍል ይወጣል። የማሳከክ ወይም የህመም ስሜት እንደሌለውም ዶክተር አደራጀው አስረድተዋል። • ማድያት በላይኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ነጣ ወይም ጠቆር ያለ ቡናማ የሆነ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አመላክተዋል። • ማድያት በውስጠኛው የቆዳ ክፍል ላይ ሲከሰት፡- ሰማያዊ ግራጫ ወይም ጠቆር ያለ ግራጫ የቆዳ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይ አንስተዋል። • ማድያት በሁለቱም የቆዳ ክፍሎች ላይ ሲከሰት፡- የተቀላቀለ የቡናማ እና ግራጫ ቀለም ለውጥ እንደሚያሳይም ባለሙያው አብራርተዋል። 👉 ማድያት ያለበት ሰው ምን ዓይነት ጥንቃቄዎችን ማድረግ ይገባዋል? 1ኛ. ወርቃማ ጥንቃቄ፡- • ተከታታይና ጥብቅ የሆነ የፀሐይ መከላከያ መጠቀም ይገባል ይላሉ የሕክምና ባለሙያው። በዚህም መሠረት ከቤት ከመውጣት ከ20 እስከ 30 ደቂቃ ቀደም ብሎ የፀሐይ መከላከያ ክሬሞችን መቀባትና በሁለት ሠዓት ልዩነት እየደረቡ መቀባት። • በሌላ በኩል ከ4 እስከ 10 ሠዓት ያለው የፀሐይ ሙቀት ለቆዳ ህመም አጋላጭ መሆኑን በመገንዘብ ከፀሐይ መከላከያ ክሬም በተጨማሪ ጥላና ኮፍያን መጠቀም እንደሚገባ መክረዋል። 2ኛ. ቆዳን የሚያስቆጣ የቆዳ እንክብካቤ (መስተካከል ያለበት ልማድ)• ቆዳን የሚያስቆጡ መታጠቢያዎች(ሳሙናን ጨምሮ ሌሎችም) እንዲሁም መዋቢያዎችና የሚቀቡ ነገሮች (ኮስሞቲክስን ጨምሮ ሌሎችም) አለመጠቀም ይገባል ይላሉ። • ለቆዳ ተስማሚ የሆኑ ማለስለሻዎችን በደንብ መጠቀም እንደሚገባም ይመክራሉ። 3ኛ. በሐኪም የታዘዙ መድኃኒቶችን በአግባቡ መጠቀም • በሐኪም የታዘዘ መድኃኒትን በአግባቡ(ሳያቆራርጡ) መጠቀም እንደሚመከር ያስረዱት ዶክተር አደራጀው፤ እንደ ማድያቱ እና እንደ ሰዎቹ ቆዳ ዓይነት መድኃኒቱ ለውጥ የሚያሳይበት ጊዜ ስለሚለያይና ከ8 እስከ 12 ሣምንት ሊወስድ ስለሚችል ታግሶ በደንብ ቢጠቀሙ መልካም ነው ይላሉ። 4ኛ. የተለያዩ የሕክምና አማራጮችን መጠቀም• የሕክምና ባለሙያው እንደሚመክሩት፤ በዘርፉ ያሉ የተለያዩ የሕክምና ዓይነቶችን ለምሳሌ እንደ ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ ያሉትን በሐኪም ምርመራ መሠረት መጠቀም ይገባል። 5ኛ. ከወሊድ መቆጣጠሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የተከሰተ ማድያት ከሆነ ከሕክምና ባለሙያ ጋር በመመካከር ሌላ አማራጭ መጠቀም እንደሚገባም አንስተዋል። እንዲሁም ጭንቀትን መቀነስ እንደሚገባ መክረዋል። 👉 የማድያት ሕክምናን በተመለከተ የማድያት ሕክምና በጣም አስቸጋሪ ከሚባሉትና ረጂም ጊዜ ከሚወስዱ እንዲሁም በመመላለስ ከሚያስቸግሩ የቆዳ ሁኔታዎች አንዱ መሆኑን ዶክተር አደራጀው ገልጸዋል። በሕክምና ማድያቱ የጠፋላቸው ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠው፤ በሌላ በኩል በሕክምና ሂደት የማድያቱ ሁኔታ ከነበረበት እየቀነሰ ለውጥ የሚታይበት ሁኔታ አለ ብለዋል። ይህን ለውጥ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ማስቀጠል እንደሚገባም ይመክራሉ። እንክብካቤው ከተቋረጠ ግን ማድያቱ እንደገና የሚመለስበት ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበዋል። 👉 የማድያት ሕክምና አማራጮች የሚቀቡ መድኃኒቶች፣ የሚዋጡ መድኃኒቶች፣ ሌሎች የሕክምና አማራጮች(ኬሚካል ፒልስ፣ የቆዳ ሕክምና እና ማይክሮ ኒድሊንግ)፣ የፀሐይ መከላከያ አማራጮችን በአግባቡ አዘውትሮ መጠቀም እንደሚገባ ይመክራሉ።
በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ  7 ቀናት የሚኖሯት ጳጉሜን…
Sep 5, 2025 1731
ጳጉሜን በሦስት ዓመታት አምስት፣ በአራት ዓመታት ውስጥ ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት ውስጥ አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት ይኖሯታል። 👉 ‘ጳጉሜን’ ማለት ምንድን ማለት ነው? ‘ጳጉሜን’ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል መምጣቱን በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮትና የሥነ-ልቡና መምህር አባ ጌዴዎን ብርሀነ ይገልጻሉ። ትርጉሙም “ተውሳክ ወይም ተረፍ” ማለት መሆኑን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ አስረድተዋል። (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ላይም “በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ተጨማሪ ሆና የምትመጣ መሆኗ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት በሦስት ዓመት አምስት፤ በአራት ዓመት (በዘመነ ዮሐንስ) ስድስት እንዲሁም በ600 ዓመታት አንድ ጊዜ ሰባት ቀናት እንደምትሆን ተመላክቷል። 👉 የጳጉሜን መሠረት? ይህን በተመለከተ መምህር አባ ጌዴዎን ሲያስረዱ፤ በየቀኑ የሚተርፉ ተረፈ ደቂቃዎችና ሰከንዶች ቀናትን እያስገኙ ተጠራቅመው ከዓመቱ በስተመጨረሻ አምስት ዕለታት ይተርፋሉ ይላሉ። በዚህም ጳጉሜን የተባሉ አምስት ዕለታት እንደሚገኙ ጠቁመው፤ አንድ ዓመት ደግሞ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልኢት ይሆናል ሲሉ ይገልጻሉ። 15ቱ ኬክሮስ በአራት ዓመት ስድስት ጳጉሜንን ይወልዳል ያሉት መምህሩ፤ ስድስቱ ካልኢት ደግሞ በ600 ዓመት ሰባተኛ ጳጉሜንን ያስገኛሉ በማለት አብራርተዋል። 👉 ከጭማሬ ቀንነት በተለየ ያላት ትርጓሜ ምንድን ነው? እንደ መምህር አባ ጌዴዎን ገለጻ፤ ‘ጳጉሜን’ ከተጨማሪ ቀናትነት የተሻገረ ለኢትዮጵያውያን የማንነት ዐሻራ የእኩልነት ምልክት ናት። በዓለም ዘንድ ባለው የበላይነት እና ሌላውን አሳንሶ የማየት ዝንባሌ እንደነዚህ ያሉ የጥበብ መንገዶች የኢትዮጵያውያንን ማንነትና በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የቀዳሚነት ቦታም ከሚያሳዩ ምልክቶች መካከል አንዱ በመሆኑ የማንነት መገለጫ ናት ይላሉ። ምክንያቱም ከማንም ያልተወሰደ የራስ ማንነት መኖሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን በዓለም ዘንድ የነበራቸውን የመፈላሰፍ፣ የስልጣኔና አካባቢያቸውን በንቃት የመገንዘብ አቅም የሚያሳይ ስለሆነ ብለዋል። ጳጉሜን ኢትዮጵያን ከቀደምት ስልጡን ሀገራት መካከል ቀዳሚ የስልጣኔ ፋና የፈነጠቀባት ለመሆኗ ማሳያ ስለመሆኗም ይናገራሉ። የሰው ልጅ አካባቢውን በንቃት መገንዘብ መጀመሩ እና የሰማያዊ አካላትን የማይዋዥቁ ክስተቶች በመከታተል የማይታየውንና የማይሰፈረውን የጊዜ ርዝማኔ በብርሃናት እየሰፈረና እየለካ፤ ዕለታትን፣ ሳምንታትን፣ ወራትን፣ ወቅትን፣ ዓመታትን፣ አዝማናትን እና ሌሎች ዐውዳትን መቀመሩን ጠቅሰዋል። በዚህም የጊዜ ልኬት ከሥነ-ፈለክ እና ከሐሳበ-ከዋክብት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ እንዲሆን አድርጎታል ነው ያሉት። በአጭሩ ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን ከሚያዩአቸው ተደጋጋሚ ሁነቶች በመነሳት የጊዜ አሃዶችን ወስነዋል፤ ክፍፍሎችንም በይነዋል ብለዋል መምህር አባ ጌዴዎን። በተለይም ለዕይታቸው ቅርብ የሆኑት የፀሐይ እና የጨረቃ ያለማቋረጥ መውጣት እና መግባት፣ የሚወጡበት እና የሚገቡበትም የጊዜ መጠን በአንጻራዊነት ቋሚ በመሆኑ ለቀን አቆጣጠራቸው ዋነኛ ግብዓቶች እንደሆኗቸው ተናግረዋል። በሂደትም የዑደታቸውን የጊዜ መጠን በሚገባ ተረድተው፣ የዑደታቸውን ህጸጾች ዐወቁ ይላሉ። በዚህ ብቻ ሳይገደቡ የሰማይ አሰሳን ከፀሐይ እና ጨረቃ ወደ ሌሎች አፍላካት፣ ወደ ከዋክብትም ጭምር ማስፋታቸውን ነው የሚገልጹት። በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ የራሳቸው የቀን መቁጠሪያ ቀመር ካላቸው ቀደምት ሀገራት መካከል አንዷ መሆን መቻሏን አስገንዝበዋል። ለዚህም በዋቢነት ከሚጠቀሱት ጥንታዊ መዛግብቶቿ መካከል መጽሐፈ ሄኖክን እና አቡሻኽርን አንስተዋል። 👉 ከነበረው ወደ ሌላኛው ዓመት መሻገሪያ እንደመሆኗ ሰዎች በዚህ ወቅት ምን አይነት ሥነ-ልቡናዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ይመከራል? ጊዜ የለውጥ መስፈሪያ (መለኪያ ወይም መለያ ድንበር) መሆኑን የሚገልጹት መምህር አባ ጌዴዎን፤ ለውጥ ያለጊዜ፣ ጊዜም ያለ ለውጥ አይሆኑም፤ ትርጉምም የለውም ይላሉ። ጊዜ በዚህ ዓለም የማይቋረጥ ሂደት፤ የማይቆም የለውጥ ጥያቄ መሆኑንም ያስገነዝባሉ። በዚህ የለውጥ ምክንያት የሰው ልጅ የሚኖረው ከተሰጠው ወይም ካለው እየቀነሰ እንጅ እየጨመረ እንዳልሆነም ይጠቅሳሉ። ስለዚህ ጳጉሜን የማንቂያ ደወል ናት፤ የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ አዲስ ዘመን በለውጥ ምክንያት የተገኘ በመሆኑ ከነበረው የዕለታት ድምር ባሻገር አዲስ የሚል ቅጽል ይዞ መጥቷል ይላሉ። ስለዚህ ጳጉሜን ምን አዲስ ነገር አለ የሚል የሕይወት ጥያቄ አስከትላ የመጣች በልባችን ምኅዋር የምታቃጭል ናት ብለዋል። በጳጉሜን ብዙዎች በጽሞና ሆነው ራሳቸውን የሚያዳምጡባት ወደውስጥ በጥልቀት የሚመለከቱባት በመሆኗ ባለፉት ጊዜያት ያልተሳኩትን በቀጣይ ለማሳካት አዳዲስ ሐሳቦችን እና እቅዶችን በማዘጋጀት ለቀጣዩ ምዕራፍ የምታሻግር ናት በማለት ገልጸዋል።
የባሕር  በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 2536
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 2689
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።   ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል።   ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው።   የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው።   ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
ልዩ ዘገባዎች
በኢትዮጵያ ስንት ዓይነት የአዕዋፍ ዝርያዎች አሉ? 
Oct 13, 2025 314
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 3/2018 (ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአዕዋፍ ኑሮ ምቹ እና ተስማሚ ሁኔታዎች ካሉባቸው ሀገራት አንዷ ናት። በፈረንጆቹ 2024 እና 2025 የተደረጉ የጥናት ውጤቶች እንዳመላከቱት፤ በኢትዮጵያ ከ881 እስከ 926 የሚደርሱ የአዕዋፍ ዝርያዎች ይገኛሉ። ይህ አሃዝ ነዋሪ እና ፍልሰተኛ የአዕዋፍ ዝርያዎችን እንደሚያካትት በኢትዮጵያ ዱር እንስሣት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ለአዕዋፋት ኑሮ ምቹና አስፈላጊ ከሆኑ ሀገራት መካከል እንደምትመደብም ጠቅሰዋል። 639 ነዋሪዎችን እና 224 ወቅታዊ ፍልሰተኞችን ጨምሮ 926 የአዕዋፍ ዝርያዎች በኢትዮጵያ እንደሚገኙ ባሳለፍነው ነሐሴ ወር ላይ የተደረገ ጥናት ውጤት አመላክቷል ነው ያሉት። ከእነዚህ መካከል በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙት የአዕዋፍ ዝርያዎች ቁጥራቸው ከ18 እስከ 20 እንደሚደርስ ጠቁመዋል። አማካኝ የወፎች ዕድሜ እንደ ዝርያ፣ መጠን እና አካባቢ ስለሚለያይ ለሁሉም ወፎች አንድ አማካይ ዕድሜ አለመኖሩንም አንስተዋል። ትንሽ ዕድሜ የሚኖሩት የድንቢጥ ዝርያዎች መሆናቸውን ጠቅሰው አማካኝ ዕድሜያቸውም ሦስት ዓመት መሆኑን ተናግረዋል። እንደ አልባትሮስ (Albatrosses and Some Parrots) ያሉ ትላልቅ የአዕዋፍ ዝርያዎች እና አንዳንድ በቀቀኖች ለብዙ አሥርተ ዓመታት ሊኖሩ እንደሚችሉ አመላክተዋል። መጠን፣ ዝርያ እና የመኖሪያ አካባቢ በአዕዋፍ የሕይወት ዘመን ላይ ተጽዕኖ እንደሚያሳድሩም አስገንዝበዋል። በዚህም መሠረት ትልልቅ ወፎች ከትንንሽ ወፎች የበለጠ ረጅም ዕድሜ ይኖራሉ ብለዋል። እንደ ዝርያቸው የሚወሰን ቢሆንም አዕዋፋት ከቀዝቃዛ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸው አካባቢዎች ላይ መኖር እንደሚችሉም አንስተዋል። አንድ ተመራጭ የአየር ንብረት የላቸውም፤ አብዛኞቹ የአዕዋፍ ዝርያዎች የተረጋጋ፣ አስተማማኝ የምግብ አቅርቦት ለማግኘት እና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ ሁኔታዎችን የሚቸር የአየር ሁኔታን ይመርጣሉ ነው ያሉት። በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁ 11 ሺህ 100 የሚጠጉ የአዕዋፍ ዝርያዎች እንዳሉም ነው ያስረዱት።
በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ
Oct 11, 2025 309
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል። የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው። በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው። ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።   በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል። አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል። ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል። በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት። በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል። እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል። ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 6165
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 4645
  ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 54616
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 50774
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31517
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29018
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ በአልሸባብ ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገለፁ
Feb 14, 2024 25717
አዲስ አበባ፤ የካቲት 6/2016 (ኢዜአ)፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ አሸባሪው አልሸባብ ከሰሞኑ በሶማሊያ በፈፀመው የሽብር ጥቃት በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገለፁ። አምባሳደር ታዬ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት በሽብር ቡድኑ ጥቃት ምክኒያት በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት እና አካል ጉዳት ጥልቅ ሃዘን እንደተሰማቸው ገልፀዋል። በኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ እንዲሁም በራሳቸው ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ለሶማሊያ መንግስት እና ህዝብ የገለጹት ሚኒስትሩ ፤ በልምምድ ወቅት ወታደራዊ መኮንኖችን ኢላማ በማድረግ የተፈፀመውን ጥቃት የወንጀል ተግባር ነው ብለዋል። የወንጀል ተግባሩን ኢትዮጵያ በፅኑ እንደምታወግዘውም ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል። ጥቃቱ አልሸባብ የሽብር ቡድን በሶማሊያ እና በክፍለ አህጉሩ ደህንነት አደጋ መደቀኑን በግልፅ ያረጋገጠ መሆኑን በመግለፅ ፥ የአካባቢው ሀገራት በፀረ ሽብር የሚያደርጉትን ትብብር ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አመልክተዋል። የሶማሊያን ሰላም እና ደህንነት በጋራ ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ትብብሯን አጠናክራ በቁርጠኛነት እንደምትቀጥልም ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት ማስታወቃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።    
በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ ይፈጸማል-ባለስልጣኑ
Apr 6, 2023 24243
አዲስ አበባ መጋቢት 28/2015(ኢዜአ)፡ በአዲስ አበባ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ገለጸ። የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ የሚፈፀምበትን የድርጊት መርሐ ግብር በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በአዲስ አበባ ተወያይቷል።   የውይይቱ ዓላማ በመዲናዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎችና ኩባንያዎች በአሰራሩ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል መሆኑ ተነግሯል። በዚህ ወቅት የነዳጅና ኢነርጂ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሳህረላ አብዱላሂ፤ ባለስልጣኑ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህም ቀደም ብሎ ከነዳጅ ማደያና አከፋፋይ ኩባንያዎች ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው፤ አሁን ደግሞ ለሙሉ ትግበራው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ውይይት ተደርጓል ብለዋል። በአዲስ አበባ የኤሌክትሮኒክስ የክፍያ ስርዓቱ በአማራጭነት ለሙከራ እየተተገበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈጸም ተናግረዋል። በመሆኑም ህብረተሰቡ ማንኛውም የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ብቻ የሚፈጸም መሆኑን ተገንዝቦ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ በአስገዳጅነት እንደሚተገበርም ጠቁመዋል። በኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ሞባይል መኒ ኦፊሰር ብሩክ አድሃነ፤ የነዳጅ ግብይትን በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች በማድረግ ረገድ በቴሌ ብር ውጤታማ ስራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም ባለፉት ዘጠኝ የሙከራ ወራት በቴሌ ብር ብቻ ከ30 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ ግብይት መፈጸሙን አንስተዋል። የነዳጅ ግብይቱን በአግባቡ በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ለማከናወን የሚያስችል ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መገንባቱንም እንዲሁ። የኢትዮጵያ ነዳጅ ማደያዎች ማኅበር አባል የሆኑት አቶ ሚካኤል ገብረስላሴ እና የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ የነዳጅ ግብይት ስርዓቱ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ መንገዶች ብቻ መሆኑ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው ብለዋል። በተለይ ለነዳጅ አዳዮች ጥሬ ገንዘብ በመቁጠር የሚያባክኑትን ጊዜ ከመቅረፍ አንፃር እንዲሁም በማደያዎች የሚቀመጥ የግብይት ገንዘብ እንዳይኖር በማድረግ የደህንነት ስጋትን እንደሚፈታ ተናግረዋል። በተጨማሪም መንግስት የነዳጅ ምርት ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለውን ስርጭት ሂደት መረጃ እንዲኖረው እና ነጋዴዎችም ግብርና ታክስ እንዳያጭበረብሩ በማድረግ ቴክኖሎጂው ትልቅ ሚና አለው ነው ያሉት።  
በልጆቿ የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነትን ሳትራብ ዘመናትን የተሻገረች-ኢትዮጵያ
Mar 1, 2023 24023
በቀደሰ ተክሌ (ሚዛን አማን ኢዜአ) ነፃነት የሰው ልጅ ከፈጣሪ ከተቸሩት ፀጋዎች አንዱና ዋነኛው ነው፤ በራስ ፈቃድ መወሰን፣ በራስ መሻት መከወንና በራስ ማንነት መኖር የሰው ልጅ የነፃነት አብነቶች ናቸው። ፈጣሪ ይህን ፀጋ የቸረው ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ነው። ይሁን እንጂ ይህን ከፈጣሪ የተቸረውን ነፃነት በራሱ በወገኑ የመነጠቅ ዕጣ ፈንታ መግጠሙ አልቀረም፤ ነፃነቱን በራሱ ወገን እየተነጠቀ በራስ ፈቃድ መወሰን የማይችል እንዲሆን ተደረገ። ጥቁር ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን በነጮች ዘንድ የባርነት ግብር ተሰጣቸው። ቅኝ መግዛት ለእነሱ የኃያልነት መገለጫ አድርገው መረጡ። በዚህም አፍሪካን ተቀራምተው የራሳቸው አደረጉ። ያኔ ቅኝ ግዛት አስተዳደር ዘመናቸው በራስ እምነት መቆም፣ በራስ ባህል፣ ወግና ማንነት መኖር አይታሰብም። የሰው ልጅ ከቆዳ ቀለም ልዩነት በስተቀር በራሱ አምሳል ለተፈጠረው ሰው ተገዥ ይሆን ዘንድ አውሮፓውያን ከእኛ ውጭ ሰው ብለው በግዞት የያዟቸውን አገሮች ዜጎች የስቃይና የመከራ ህይወት እንዲያሳልፉ ፈረዱ። ከባዱን የባርነት ቅንበር በጫንቃቸው ላይ ጫኑ። ማንነታቸውን አስረስተው ያሻቸውን አደረጉ። የቅኝ አገዛዝ ገፈት ቀማሽ እንድትሆን ፅዋ የደረሳት የጥቁሮች ፈርጥ ኢትዮጵያ ግን እንዲህ በቀላሉ ለቅኝ ገዥዎች እጅ አልሰጠችም። ሰውን በሰውነቱ ብቻ የምታከብረው ኢትዮጵያ የልጆቿ ነፃነት በማንም ቁጥጥር ስር እንዲወድቅ አልፈቀደችም።ኢትዮጵያን አፅንቶ ያቆማት በመከባበርና በአብሮነት ላይ የታነፀ ባህል፣ እሴት፣ ወግና ሥርዓት በባዕዳን እጅ ወድቆ ከሚከስም ''እኛ እንቅደም'' የሚል ጠንካራ የሀገር ፍቅርና ወኔ በአበራኮቿ ክፋይ ልብ ውስጥ እንደ አቶን እሳት ተንቀለቀለ። በፈጣሪያቸው እንጂ በምድራዊ ኃይል የሚመኩ አይደሉምና ቅኝ ሊገዛቸው የመጣን የውጭ ወራሪ ኃይል በጀግንነት ታግለው የኢትዮጵያን አንድነት፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና ለማስከበር በአንድ ልብ ወስነው ቀፎው እንደተነካበት ንብ ወደ አውደ ገባሩ ተመሙ። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ኃይል፤ ወኔና ሞራልን ትጥቃቸው አድርገው በዓድዋ ተራራ እስከ አፍንጫው ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ገጠመ። ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው ተፋለሙ፣ ደማቸውን አፍሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው ለእኛ ለልጆቻቸው ነፃነትን አወረሱ፤ ለምንምና ለማንም የማይበገረው ኢትዮጵያዊ አንድነትን ትጥቅና ስንቃቸው ያደረጉትን የኢትዮጵያውያንን ከብረት የጠነከረ ክንድ መቋቋም የተሳነው ወራሪ የኢጣሊያ ኃይል ገሚሱ የጎራዴ እራት ሲሆን፤ ቀሪው ቁስለኛና ምርኮኛ ሆነ፤ ሌላው ደግሞ እግሬ አውጣኝ ብሎ ህይወቱን ለማትረፍ እግሩ ወደመራው ፈረጠጠ። ጅግኖች አባቶቻችን ደማቸውን አፍሰው፣ አጠንታቸውን ከሰክሰው የኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት አስጠብቀውና አስከብረው የፈጣሪ ልዩ ፀጋ የሆነውን "ነፃነት" ለዛሬው ትውልድ አስረከቡ። ኢትዮጵያም በትውልድ ቅበብሎሽ ሉዓላዊነቷምን አፅንታ የቆመች ነፃ አገር ሆና ቀጠለች። በዘመኑ የነበረውን ጥቁር ነጭን ማሸነፍ አይችልም የሚለውን አስተሳሰብ በሀገር ፍቅርና ወኔ ወራሪውን የፋሽሽት ኢጣሊያ ኃይል በጦር በጎራዴ አርበድብደው ድል በመንሳት ጥቁር ነጭን ማሸነፍ እንደሚች በቅኝ ገዥዎች የአገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ለነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተግባር አረጋገጡ። በደማቸው ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ የአርነት የታሪክ ድርሳን ጻፋ። በዘመን ጅረት የማይወይብ ታሪክ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በዓድዋ ተራሮች ላይ ተጻፈ። ኢትዮጵያ በልጆቿ አንድነትና የጀግንነት ተጋድሎ ነፃነት ሳትራብ ዘመናትን ተሻገረች። የነፃነት ዓርማ ሆና ለአፍሪካውያን ታየች። የዓድዋ ድል በቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ስር ወድቀው ይሰቃዩ የነበሩ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች በተለይም አፍሪካውያን የአርነት ትግል አድርገው የግፍ፣ የስቃይና የመከራ ቀንበርን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው እንዲጥሉ የፃነት ተምሳሌት ሆነ። በኢትዮጵያ የተለኮሰውን የነፃነት ችቦን አቀጣጥለው ብርቱ የአርነት ተጋድሎ አደረጉ፤ በዓድዋ ድል ከቅኝ ገዥዎች መዳፍ አፈተለኩ። የጥቁር ጭቁን ህዝቦች ነፃነት በዓድዋ የድል ገድል ለዓለም ታወጀ። አፍሪካውያን በራሳቸው ቋንቋ በነፃነት መናገር፣ በራሳቸው ባህል፣ወግና ሥርዓት እንዲሁም በራሳቸው መሪ ወደ ሚተዳደሩበት ምዕራፍ ተሸጋገሩ።የዓድዋ ድል ነገሮች አልጋ በአልጋ ሆነው በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ኢትዮጵያውያውያ ለሀገራቸው ባላቸው ቀናሂነትና ከብረት በጠነከረ አንድነትና በጀግንነት ተጋድሎ ተጋምዶ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ትግል እንጂ። የዓድዋ ድል ዛሬም ወደ ጀመርነው የልማት፣የዕድገትና የብልፅግና ማማ ላይ የሚያደርሰን መሰላል ነው። ይህ የሚሆነው ግን የአንድነት ኃይል ከጀግንነት ወኔ ሳይነጣጠል ፀንቶ ሲቆይ ብቻ መሆኑ እሙን ነው። ቀደምት አባቶቻቸን የዓድዋ ከፍታን በክብር መቆናጠጥ የቻሉት ዘር እየቆጠሩ ሳይሆን በኢትዮጵያዊ አብሮነትና አንድነት ተጋምደውና ተሰናስለው ነው። ያላቸውን የአንድነት ኃይል ተጠቅመው ድልን ተጎናጸፉ። በየዓመቱ ዓድዋን መዘከር ራስን ''እኔስ ምን ማድረግ እችላለሁ?'' በሚል እሳቤ ከሆነ ዓድዋ ህያው ነው፤ ወደ አለምነው የስኬትና የብልፅግና ከፍታ ላይ የአንድነታችን ኃይሉ እንደሚያደርሰን እሙን ነው። እንደ ቀደምት አባቶቻችን በተጋመደ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በማጠናከር በኢኮኖሚው፣ ማኅበራዊ፣ በፖለቲካው ያሉ ፈተናዎችን በሀሳብ ልዕልና በማሸነፍ ለሌላ ድል መትጋት አለብን። አንድነታችንን በማፅናት በኅብረት ለኢትዮጵያ ከፍታ መትጋት ከሁላችንም ይጠበቃል።"ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲ ሀገራዊ ብሂሉ ከተባበርን የማናልፈው ፈተና አይኖርም። አንዴ በጦርነት ሌላ ጊዜ በድርቅና በሌሎች መንስኤዎች ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች በአብሮነት ተጋፍጠን ድል እያደረግን መጥተናል። ፈተና ሁሌም ይኖራል፤ ማሸነፍና መሸነፍ ግን በእኛ ፅናትና ጥንካሬ ይወሰናል። ለወደፊትም የሚያጋጥመንን ፈተና አንድነታችንን አፅንተን ኅብረታችን ለሀገራችን ልማት፣ ዕድገትና ብልፅግና በማዋል በርካታ ዓድዋዎችን እንሰራለን። የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጥቁር ጭቁን ህዝቦች የኩራት ምንጭ የነፃነት ዓርማ ነው። የዓድዋን ታሪክ መጠበቅና መደጋገም የእኛ የኢትዮጵያውን ኃላፊነትና ግዴታ ነው። ልዩነትን መስበክ ከኢትዮጵያዊ ከፍታ መሸራተት ነው። እኛነትን ረስቶ እኔ ማለት የዓድዋን ታሪክ መሸጥ ነው። ኢትዮጵያውያን አንድ ሆነን እንጂ ተከፋፍለን የሰራነው ታሪክ የለም። የትናንት መልካም ስምና ዝና ከዘመኑ ጋር አብሮ ከፍ ከፍ እያለ አብቦ ማፍራት እንጂ፤ በልዩነት አስተሳሰብና አመለካከት ሊኮሰምን አይገባም። የኢትዮጵያውያን የአንድነትና የሉዓላዊነት መገለጫ፣ የዓለም ጭቁን ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌ-ዓድዋ ለዘላለም በክብር ሲዘከር ይኖራል‼  
ለላቀ ውጤት - የተማሪ መምህርና ወላጆች ጥምር ጥረት
Mar 27, 2023 23842
በሃብታሙ ገዜ ስልጡን የመንገድ ጠበብቶች በጥንቃቄ የከተማ ውብ ገፅታ አልበሰው ባነጿት ከዚራ አካባቢ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አዳራሽ በሰው ተሞልቷል። የተሰበሰቡት ወጣት ተማሪዎች፣ የድሬደዋ አመራሮች፣ የትምህርት ዘርፍን የሚመሩ አካላትና ወላጆች በፈገግታ ተሞልተዋል። ይበልጥኑ ከወጣቶቹ ገፅታ የሚንፀባረቀው የደስታ ፈገግታ ለአዳራሹ የተለየ ብርሃን ደርቦለታል። የደስታቸው ምንጭ ደግሞ አምና የተፈተኑትን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በላቀ ውጤት አልፈው ሽልማት በመቀበል ላይ መሆናቸው ነው። የአዳራሹን የሽልማት መርሃ ግብር የሚመራው ሰው ድንገት "የዛሬው ልዩ ክስተት ከሚሸለሙት ተማሪዎቻችን መካከል ከ600 በላይ ውጤት በማምጣት ከወንድሞቿ ጋር ሦስት ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ የአንድ ቤተሰብ አባላት መገኘታቸው ነው" ሲል ተናገረ። ይሄኔ አዳራሹ በጭብጨባ ተናጋ፤ ሁሉም ተሰብሳቢ በአንድነት ቆሞ ጭብጨባውን አቀለጠው። ለሽልማት ወደ አደባባዩ የመጡት በደስታ ፀዳል የወረዙት የወላጅ ተወካይ እንጂ የድሉ ባለቤት የሆኑት እነዚህ ሦስት ተማሪዎቹ አይደሉም። በአዳራሹ የተሰባሰቡት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃርና የካቢኔ አባላት እንዲሁም ተሸላሚዎቹ ተማሪዎች "የዓመቱ የተለየ ክስተት የሆኑትን ተማሪዎች" ለማየት ዓይኖቻቸው ቢባዝንም አልተሳካም። ለምን ካላችሁ ተማሪዎቹ ወደ ተመደቡበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጓዛቸው ነው። የመድረኩ የድምፅ ማጉያ ባለቤትም ሆነ ተሰብሳቢዎቹ የዓመቱ ክስተት የሆኑት ኒያ ሰላሃዲን 602፤ አሊ ሰላሃዲን 556፣ አማን ሰላሃዲን 526 ያመጡት ተማሪዎች መንትዮች መሆናቸውን ቢያውቁ ኖሮ አዳራሹ ሌላ የግርምት ደስታን ባስተናገደ ነበር። ሽልማቱን ያበረከቱት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ተሸላሚዎች በጥረታቸው በትጋታቸው ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን አብስረዋል። አገር በዜጎች አንድነትና መተባበር እንደሚፀናው፤ የተማሪዎች ውጤትም በተማሪዎችና በመምህራን ጥረት ብቻ ሳይሆን በወላጆች ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ ጭምር የሚመጣ ነው። "በተለይ ከአንድ ቤተሰብ የበቀሉት ተማሪዎችና የዛሬው ሽልማት እና ውጤት ያስተማረን ይህንኑ ነው" ብለዋል ከንቲባው። በዚህ አደራሽ ውስጥ የሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ርዕሰነ-መምህራን ታድመዋል። እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ከተፈተኑት ከ3 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች መካከል በቀጥታ ያለፉት 250 ተማሪዎች ብቻ ናቸው። ለመጣው ውጤት ተሞጋሹም ተወቃሹም የዘርፉ አመራሮች፣ ተማሪዎች፣ መምህራንና ወላጆች ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሙሉካ መሐመድ "ለመጣው ዝቅተኛ ውጤት በትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለነው በሙሉ ተጠያቂዎች ነን" ብለዋል። ኃላፊዋ ሌላውም ከዚህ ትምህርት መውሰድ እንዳለበት ነው የገለጹት። እንደ አስተዳደሩም የትምህርት አመራሮች፣ ርዕሳነ መምህራን፣ መምህራንና ወላጆች ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ እንቅስቃሴ መጀመሩን አውስተዋል። በመንግስት የ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ከኩረጃ ነፃ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ ተማሪዎች በጥረታቸውና በብቃታቸው የልፋታቸውን ውጤት እንዲያገኙ ያስቻለ ነው። የፈተና አሰጣጡና ውጤቱ እንደአገር ያለንበትን አዘቀት አስተምሮ ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ፤ ብቁና በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማዋለድም ጥርጊያ መንገድ ሆኖ አልፏል ማለት ይቻላል። መንግስት የትምህርት ጥራትን ከታችኛው እርከን ጀምሮ ለማረጋገጥም በዘርፉ ሙሁራን ጥልቅ ጥናት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ መሠረት ያደረገ ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ዘንድሮ እስከ 8ተኛ ክፍል ተግባራዊ አድርጓል። ለመማር ማስተማሩ መጻህፍት ተዘጋጅተው ለመምህራን ስልጠና በመስጠትም ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል። በሚቀጥለው ዓመትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው። በሽልማት ሥነስርዓቱ ላይ እንደታየው ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች ሚና የጎላ ነው። ወላጆች ተገቢውን ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል ካደረጉ የሚፈልገው ለውጥና ውጤት ማምጣት ይቻላል። ወይዘሮ ሙሉካ በአትኩሮት ከገለጹት ሃሶቦች መካከል ዋናዎቹን ሰበዞች መዝዤ፤ "ተጠያቂዎቹ እኛው ነን" የሚለውን ሃሳብ አንግቤ ለድሬዳዋና ለአገር ከፍ ሲል ለዓለም ህዝብ ጭምር በየዘርፉ ታላላቅ ሙሁራን ወደ አፈሩት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አመራሁ። ድንገት ሃሳቤን ቀለበስኩት። መነሻዬ የወላጆች ኃላፊነት እና ድጋፍ መሆኑን መርሳት ዞሮ ዞሮ የምፅፈው መዳረሻ መርሳት ይሆንብኛል ብዬ ነው። እናም ወደ ሦስቱዎቹ፤ የዓመቱ ክስተቶች አባት አመራሁ። ድሬዳዋን ለሁለት እኩሌታ የሚከፍላትን የደቻቱን ድልድይ ተሻግሬ ወደአንድ የግል የሕክምና አገልግሎት መስጫ ሆስፒታል ገባሁ። አምሮ በተሰናዳው ሆስፒታል ውስጥ ሙያዊ ኃላፊነታቸው እየተወጡ አገኘኋቸው፤ የማህፀንና የፅንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍን። የውጤታማ ተማሪዎቹ ወላጅ ናቸው፤ በ1970 ዎቹ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መዝለቅ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል በሚቆጠርበት ዘመን በከፍተኛ ማዕረግ አልፈው በቀሰሙት ዕውቀትና ጥበብ የሰዎችን ሕይወት እየታደጉ ይገኛሉ። ዶክተር ሰላሃዲን ለትምህርት ጥራት መውደቅ ወደ ዩኒቨርሲቲ በስርቆትና ኩረጃ የመግባት ዝንባሌዎች እንደሆኑና ይሄም ሁሌም የሚያንገበግባቸው ጉዳይ መሆኑን አጫወቱኝ። መንግስት በተለይ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ባልደረቦቻቸው በሁለተኛ ደረጃ የፈተና አሰጣጥ ላይ የወሰዱት እርምጃ አስደስቷቸዋል። "በተለይ ተማሪዎች በትምህርት ቤት ከሚያሳልፉት ጊዜ በበለጠ ከወላጆቻቸው ጋር ያላቸው ጊዜ ይበልጣል። ከሁሉም ነገር በላይ ለትምህርት ትኩረት ማድረጋቸውን መከታተልና መደገፍ የኛ ፋንታ ነው፤ አንዴ መስመር ከያዙ የሚመልሳቸው ችግር አይኖርም" ይላሉ። ሦስቱ ልጆቻቸውን በዚህ መንገድ በመደገፍ እና ከትምህርት ቤታቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ አስችለዋል። 604 ያመጣችው ስኮላርሽፕ ሺፕ አግኝታ ወደ ውጭ ሄዳለች፤ ሁለቱ ደግሞ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ናቸው። "ለልጆቼ የፈለጉትን የማድረግ አቅም ቢኖረኝም ያለትምህርት የሚፈጠር አንዳች ነገር እንደሌለ ገብቷቸው ለውጤት በቅተዋል" ይላሉ ዶክተር ሰላሃዲን። ብዙ የመስራት እንጂ ብዙ የመናገር ዝንባሌ የማይታይባቸው እኚህ የታታሪዎች አባት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እና ውጤታማ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚደረግ ጥረት የወላጆች ክትትልና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ነው በአፅንኦት ያሳሰቡት። "የሽልማቱ መርሃ ግብር ወደሌላ አካባቢ በሄድኩበት አጋጣሚ በመካሄዱ ሳልገኝ ቀረሁ፤ በጣም የቆጨኝና ቅር ያለኝ ዕለት ሆኖ አልፏል" ብለዋል። እሳቸውን ጨምሮ አንቱ የተሰኙ ሙሁራን ያፈራው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ፍቃዱ ሰንበቶ፤ የማርያም ሰፈር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ኢጀታ መኮንን ካለፈው ክፍተት በመማር ዘንድሮ የተሻለ ውጤት እንዲመጣ የተማሪዎች አመለካከት ላይ ለውጥ እና እችላለሁ የሚል መርህ የማስረጽ ሥራ ተሰርቷል ብለውኛል። ለውጤቱ ቀዳሚ ባለቤት ተማሪዎች ቢሆኑም ከወላጆቻቸው ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የተለያዩ የማካካሻና ለፈተና ዝግጁ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ነው ርዕሳነ መምህራኑ የገለጹት። ቅኝቴን በመቀጠል ሽቅብ ወደ ሳብያን ሁለተኛ እና የመሰናዶ ትምህርት ቤት አመራሁ። ይህ ትምህርት ቤት በከተማዋ ካሉት ትምህርት ቤቶች በውጤታማነት እና በብዛት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማሳለፍ ረገድ ወደር አልነበረውም፤ ባለፉት ዓመታት። ከተመሠረተ 22 ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ ትምህርት ቤት በምክትል ርዕሰ መምህርነት የሚመሩት አቶ በፍቃዱ ወልደሰማያትን አገኘኋቸው። ትምህርት ቤት በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተናቸው ከ800 በላይ ተማሪዎች መካከል ያለፉት 20 ናቸው። የመጣው ውጤት ያለንበትን ደረጃ ፍንትው አድጎ ያሳየን መሆኑን ተከትሎ መሠረታዊ የሆኑት ችግሮች በጋራ ተነቅሰው ለመጪው ጊዜ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የጋራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደ ሥራ ተገብቷል። አቶ በፍቃዱ እንዳሉት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትምህርት ቤቱን ሞዴል ትምህርት ቤት ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን ለዘንድሮው ተፈታኞች ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው። እነዚህን ሥራዎች የተማሪ፣ መምህርና ወላጅ ህብረት በቅርበት እንዲከታተል ተደርጓል። ለተማሪዎች ውጤት ማማር የወላጆች የቅርብ ክትትልና ደጋፍ መሠረታዊ ጉዳይ ነው የሚሉት አቶ በፍቃዱ፣ ለዚህ ጉዳይ ትምህርት ቤቱ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው ነው የገለጹት። "በተለይ ወላጆች በትምህርት ውጤታማነት ላይ ሚናቸውን እንዲወጡ ልክ እንደ ዶክተር ሰላሃዲን አይነት ቤተሰቦች ተሞክሮ የማስፋት ሥራ ለመስራት ትምህርት ቤቱ አቅጣጫ አስቀምጧል" ብለዋል። "ፍቃደኛ ከሆኑ የመጀመሪያው እንግዳችን ዶክተር ሰላሃዲን በማድረግ ለወላጆች ህብረት ተሞክሮን እንዲያካፍሉ እናደርጋለን " ብለዋል። በድሬዳዋ ታሪክ ከፍ ሲልም እንደ አገር በ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ1990 ዎቹ ዘመን ጀምሮ እንዲህ አይነት ዝቅተኛ ውጤት አለመምጣቱን የሚገልጹት ደግሞ የትምህርት ቤቱ አንጋፋ መምህር እዮብ ረታ ናቸው። የፊዚክስ መምህሩ እንደሚሉት የአምናው ክፍተት በሰከነ መንፈስ ታይቶ ዘንድሮ የተሻለ ሥራ ለመስራት መምህራን በጥሩ መንፈስ ጉዞ ጀምረዋል። ወላጆችም ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት መላክ ብቻ ሳይሆን የዕለት ተዕለት ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ነው የገለጹት። "የተማሪዎች የትምህርት ቤት ቆይታ ለሰዓታት ብቻ የተወሰነ መሆኑን በመረዳት ወላጆች በስነ ምግባር የታነፀ በራስ የሚተማመን ዜጋ ለማፍራት የተጀመረውን ጉዞ መደገፍ አለባቸው" በትምህርት ቤቱ የዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪ ረደኤት ገነሙ በበኩሏ "እንደአገር በዩኒቨርሲቲዎች የተጀመረው የፈተና አሰጣጥ ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ ጥረት ውጤት ለማምጣት የሚተጋ ትውልድ ለመፍጠር ያግዛል" ብላለች። በትምህርት ቤቱ የተጀመረው ልዩ ዕገዛ መጠናከርና መቀጠል እንዳለበት የምትገልጸው ተማሪ ረድኤት ወላጆቿ ተገቢውን ድጋፍ ከማድረግ በተጨማሪ ከመምህራን ጋር የጠበቀ ግንኙነት በመፍጠር የልጆቻቸውን ትምህርት ሊከታተሉ እንደሚገባ አውግታኛለች። እኔም ሆንኩ የዘንድሮ ተፈታኞች ትምህርት ቤታችንንና ድሬዳዋን በውጤት ለማስጠራት ጠንክረን እያጠናን ነው ብላለች። ከገጠር ከተማ ተጉዞ የሚማረው የድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪ አላሙዲን አልይ በበኩሉ፤ መንግሥት የፈተና ኩረጃን ለማስቀረት የጀመረውን ተግባር ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ነው የገለፀው። "የዘንድሮ የመምህራን ድጋፍ የተለየ ነው፤ እኛም ልዩ የጥናት ጊዜ እንዲጀመር ጫና እየፈጠርን ነው፤ ወላጆቼም በአቅማቸው እየደገፉኝ በመሆኑ ቀሪው ሥራ የኔ ጥረትና ብርታት ይሆናል፤ ልፋቴ ውጤት እንዲያስገኝ የስርቆትና የኩረጃ ሂደት መወገድ አለበት" ብሏል ተማሪ አላሙዲን። ከሳብያን ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ግቢ ለቅቄ ስወጣ ዶክተር ሰላሃዲን ዩሱፍ ያሉኝ ትዝ አለኝ። "ለተሞክሮ የሚሆን ነገር እኔ ጋር ካለ ያለችኝን ጊዜ አብቃቅቼ ለዘንድሮው ተፈታኞች ሃሳቤን ለማካፈል ዝግጁ ነኝ" ያሉኝ በአዕምሮዬ ደጋግሞ እያቃጨለብኝ ጉዞዬን ቀጠልኩ። ለመውጫ ያህል፤ በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ በመንግሥት እና በግል 22 ትምህርት ቤቶች ከ5 ሺህ በላይ ተፈታኞች በትምህርት ገበታ ላይ ናቸው። እነዚህ ተፈታኞች በራሳቸው ጥረት የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ በየአቅጣጫው የተቀናጀ ድጋፍ የማድረግ ጅምር ተግባራት ተስተውለዋል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ይህን ዙሪያመለስ ድጋፍ በማጠናከር ተማሪዎቹን ለውጤት ማብቃት በሁሉም ዘንድ ለአፍታ መዘንጋት የለበትም። መድረሻውን ለማሳመር መነሻውን አድምቶ ማበጃጀት ግድ እንደሚልም እንዲሁ።
በብዛት የታዩ
ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ ታደርጋለች - አምባሳደር ስቴፋን አወር
Jun 17, 2023 54616
አዲስ አበባ ሰኔ 10/2015 (ኢዜአ) ፦ ጀርመን በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት እንዲሳካ ድጋፍ እንደምታደርግ በአገሪቷ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስቴፋን አወር ገለጹ። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን የሰብአዊ ድጋፍ በእጥፍ ማሳደጓንም አመልክተዋል። ጀርመን ከኢትዮጵያ ጋር ግንኙነት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ በፖለቲካው፣ በማህበራዊ እና በኢኮኖሚ የትብብር መስኮች ያላቸው አጋርነት እየተጠናከረ መምጣቱን አምባሳደር ስቴፋን ለኢዜአ ገልጸዋል። ጀርመን በአቅም ግንባታ፣ በግብርና ምርታማነት እንዲሁም በማህበራዊ ልማትና በመልካም አስተዳደር ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምታደርገው የልማት ትብብር ማደጉን አመልክተዋል። ጀርመን በተለይም በልማት ኤጀንሲዋ(ጂ አይ ዜድ) በኩል ለኢንዱስትሪው እድገት ወሳኝ የሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረጓን ጠቅሰዋል። በሌላ በኩል የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ሙያዊ ድጋፍ እንዲሁም የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ነው አምባሳደሩ የገለጹት። በኢትዮጵያ ለችግር የተጋለጡ ዜጎችን ለመደገፍ ሰው ተኮር የሆኑ ፕሮጀክቶችን ለአብነትም የሰብአዊና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ጀርመን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ወደ 82 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር ከፍ በማድረግ በእጥፍ ማሳደጓንና ይሄም "ጀርመን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ ድጋፍ በማድረግ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያስቀምጣታል" ብለዋል። በሌላ በኩል ጀርመንና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ይህንንም እውን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱን አገራት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ለአብነትም በጀርመን የባህል ተቋምና በሌሎችም ኢንስቲትዩት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን በማሳየነት ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተጀመረው የሰላም ስምምነት ቀጣይነት እንዲኖረው ጀርመን ፍላጎት እንዳላት ገልጸው ለዚህም ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች ነው ያሉት አምባሳደር ስቴፋን። የኢትዮጵያ መንግሥት የሽግግር ፍትህ ለማረጋገጥ የጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን የጠቆሙት አምባሳደሩ ጀርመን ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ድጋፍ ታደርጋለች ብለዋል። ጀርመን የአፍሪካ ሕብረት እንዲጠናከር በተለይም በአፍሪካ አገራት መካከልም የፖለቲካና ምጣኔ ኃብታዊ ውህደት እንዲረጋገጥ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቁመዋል። ኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነታቸውን የጀመሩት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1905 ነው።
በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
Jun 29, 2023 50774
አዲስ አበባ ሰኔ 22/2015(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያና ሩስያ መካከል የዳበረውን ባህላዊና ኪነ ጥበባዊ ትስስር ይበልጥ ለማጎልበት እየተሰራ መሆኑ የሀገራቱ ተወካዮች ገለጹ። 'የሩስያ ባህል ቀን በኢትዮጵያ' በሚል መሪ ሃሳብ የሀገሪቱን ባህል የተመለከተ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ የሩስያ ኤምባሲ አዘጋጅነት አዲስ አበባ በሚገኘው የሩስያ የሳይንስና ባህል ማዕከል/ፑሽኪን/ ተካሂዷል። የሩስያን ባህል የሚያስቃኝ የኪነ ሕንጻ ዐውደ ርዕይ በማዕከሉ የተከፈተ ሲሆን በሁለቱ ሀገራት ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶችና ተዛማጅ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።   የኢትዮጵያና ሩስያ ታሪካዊ ግንኙነት በርካታ ምዕተ ዓመታትን ቢያስቆጥርም ይፋዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የተጀመረው ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይነገራል። 125ኛው ዓመቱን ያስቆጠረው የሁለቱ ሀገራት ዘመናትን የተሻገረ ጽኑ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት ከፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብሮች ባሻገር ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስሮችም እንደጎለበቱ ይወሳል። በኢትዮጵያ የሩስያ አምባሳደር ኢያቭገኒ ተርኪን እንዳሉት ዘመናትን በጽኑ ወዳጅነት የዘለቀው የኢትዮ-ሩስያ ዲፕሎማሲያዊ እና የህዝብ ለህዝብ ትስስር በባህላዊና መንፈሳዊ ቅርርብ ያዳበረ ነው።   በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የዳበሩ ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ኪነ ጥበባዊ እና ታሪካዊ ግንኙነቶችና ትብብሮች ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። በመጭው ሕዳር ወር ዕውቅ የሩስያ ድምጻዊያንን ያካተተ ባህላዊ የሙዚቃ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ስራውን እንደሚያቀርብ ገልጸዋል። ከዚህም በሻጋር የኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሙያተኞች ወደ ሩስያ በመሄድ የኢትዮጵያን ባህል የሚያስተዋውቁብትን ዕድል ለማመቻቸት ፍላጎት እንዳላቸውም ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው በበኩላቸው የሁለቱን ወዳጅ አገሮች ባህል ልውውጥ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያግዙ ዝግጅቶች በአዲስ አበባ ፑሽኪን ማዕከል ጋር በመተባበር እንደሚዘጋጁ ጠቁመዋል።   የኢትዮ-ሩስያ ባህላዊ ትስስር ለማጠናከር በኪነ ሕንጻ፣ በስነ ጥበብ እና በሌሎች ኪነ ጥበብ ዘርፎች ላይ በስፋት እንደሚሰራ አረጋገጠዋል። ኢትዮጵያ ባህላዊና መንፈሳዊ ቅርሶቿን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ገልጸዋል። ለአብነትም የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን የሚዘክር የአርኪኦሎጂና የቨርቹዋል ሪያሊቲ ቋሚ ዐውደ ርዕይ በላሊበላ መከፈቱን ገልጸዋል። ”ላሊበላ በእምነት የታነፀ” በሚል መሪ ሀሳብ የተከፈተው ዐውደ ርዕይ በቀጣይ ሩስያን ጨምሮ ወደ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ የመውሰድ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የሩስያ ዘመናዊ ሥነ-ጽሁፍ አባት የሚሰኘው ዕውቁ ሩስያዊ ባለቅኔ አሌክሳንደር ፑሽኪን 225ኛ ልደት በዓል በቀጣይ ዓመት በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል። በአሌክሳንደር ፑሽኪን ልደት ቀን የተሰየመው የሩስያ ቋንቋ ቀን በቅርቡ በአዲስ አበባ መዘከሩም ይታወሳል።
“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር እየተካሄደ ነው
Mar 21, 2023 31517
አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ)፦“የመደመር ትውልድ” መጽሐፍን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ የማስተዋወቅና የሽያጭ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል እየተካሄደ ነው። በኦሮሚያ ክልል ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በባሌ ዞን ለሚገኘው የሶፍ ዑመር ዋሻ የቱሪዝም መሠረተ ልማት ማስገንቢያ እንደሚውል ተገልጿል።   በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተጻፈው "የመደመር ትውልድ" መጽሐፍ በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን ሶስት ክፍሎች እና አስር ምዕራፎችም አሉት።   እየተካሄደ በሚገኘው መርሐ-ግብር ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳና የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረህማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባ ገዳዎች፣ ዲፕሎማቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።   የ"መደመር ትውልድ" መጽሐፍ ባለፈው ቅዳሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ሌሎችም እንግዶች በተገኙበት መመረቁ ይታወሳል።
ባጃጅ ውስጥ ተረስቶ ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ነው
Mar 26, 2023 29018
አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ ከተማ በሚያሽከረከረው ባጃጅ ውስጥ ተሳፋሪ ረስቶት ያገኘውን 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል። መኮንን ግርማ ኑሮውን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ በባጃጅ አሽከርካሪነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው። ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ የተለመደ ስራውን እያከናወነ ሳለ የከተማው ነዋሪ የሆኑት አቶ መሐመድ ኡስማን ከሳቢያን ኦርቢት ተብሎ ወደሚጠራው የከተማው ክፍል ለመጓዝ መሳፈራቸውን ተናግሯል። ይህ ከሆነ ከአንድ ሰዓት በኋላ “ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እንድመለከት” ተነገረኝ ይላል ወጣቱ አሽከርካሪ መኮንን። በተነገረው መሰረት ወደ ተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሮ ሲመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ 150ሺህ ብር በማግኘቱ ወዲያው ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት በማምራት ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ገልጿል። ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፤ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ኡስማን በበኩላቸው ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልጸዋል። አቶ መሐመድ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ስነ-ምግባር ያለው አሽከርካሪ እንዲፈጠር እየሰራን ያለው ስራ ፍሬ እያፈራ መምጣቱን ይህ ትልቅ ማሳያ ነው ብለዋል።
መጣጥፍ
ኢሬቻ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ማንሰራራት!
Oct 3, 2025 779
ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነው፤ ሰዎች በክረምት ወቅት ከሚከሰት መለያየትና መራራቅ በኋላ ዳግም የሚገናኙበት፣ በአብሮነት ብርሃን ለማየት ያበቃቸውን ፈጣሪ የሚያመሰግኑበት ዕለት ነው። ስለ ሰላምና አንድነት የሚዘመርበት፣ ስለመጪው ጊዜ መልካም ምኞት የሚገለጥበት፣ ሁሉን ላደረገ ፈጣሪ ምስጋና የሚቸርበት የአብሮነት በዓል ነው። ኢሬቻ የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር ያለው ጥብቅ ቁርኝት የሚገለጽበት የገዳ ስርዓት አንዱ አካል ነው፡፡ የኢሬቻ እሴቶች ጠንካራ ህብረ-ብሔራዊ አንድነት ያላት ሀገር ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው። አንድነት፣ ወንድማማችነት፣ አብሮነት፣ ሰላም፣ ፍቅር፣ ዕርቅ እና ሌሎችም ተጠቃሽ የመልካም እሴቶች መገለጫ ነው። በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የገዳ ስርዓት አንዱ እሴት ኢሬቻ ሲሆን፤ ለሀገር ማንሠራራትና ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ መሠረት ይሆናል፡፡ ኢሬቻ አብሮነት የሚጸናበት፣ የወንድማማችነትና እህትማማችነት እሴት ይበልጥ የሚጎላበት፣ አሰባሳቢ ትርክት የሚጎለብትበት፣ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው የፍቅር፣ የአንድነት እና የአብሮነት ማሰሪያ ከፍ ያለ በዓል ነው፡፡ ኢሬቻ በጋራ የሚያከብሩትና የዓለም ቱሪስቶች የሚታደሙበት ሲሆን፤ ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የኢትዮጵያ ድንቅ ባህል ጎልቶ የሚታይበት ነው፡፡ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል አከባበር ሀገራዊ ማንሰራራት በተግባር የተረጋገጠበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመርቆ ዓለም የኢትዮጵያን መቻል በተግባር ባየበትና ሌሎች ለሀገር ማንሰራራት ዕውን መሆን መሠረት የሚጥሉ ትላልቅ ሀገራዊ ኘሮጀክቶች ይፋ በተደረጉበት ማግስት መሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡   በዓሉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመላው ኢትዮጵያዊያንን ሕብረት የሚንጸባረቅበት ሆኖ በተለያዩ አከባቢዎች በድምቀት እየተከበረም ይገኛል፡፡ በልመናው፣ በምርቃቱ፣ በምስጋናው ሁሉ ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! (አሜን! አሜን! አሜን!) የሚሉ ድምፆች ይስተጋባሉ። Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Hayyee! Waaqa Uumaa, Waaqa Uumamaa ፍጥረትን የፈጠርክ ፈጣሪ Gurraacha garaa garbaa የእውነትና የሰላም አምላክ! Dogoggora nu oolchi ከስህተትና ከክፉ ነገሮች ሁሉ ጠብቀን! Dacheef nagaa kenni ለምድራችን ሰላም ስጥ! Laggeenif nagaa kenni ለወንዞቻችን ሰላም ስጥ! Olota keenyaaf nagaa kenni ከጎረቤቶቻችን ጋር ሰላም ስጠን! . . . Loowan keenyaaf nagaa kenni " ለሰውም ለእንስሳቱም ሰላም ስጥ!" በማለት ይመረቃል። ሕዝቡም ይሁንልን ይደረግልን ሲል "አሜን! አሜን! አሜን!” ይላል። የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ እንዲሁም በማግስቱ እሑድ መስከረም 25 ቀን በቢሾፍቱ ሆራ ሀርሰዲ " ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት " በሚል መሪ ሐሳብ ይከበራል። የክራምት ወራት እንዳበቃ የሚከበረው "ኢሬቻ መልካ" Irreecha Birraa (በውኃ ዳርቻ የሚከበር) ሲሆን፤ በዓመቱ አጋማሽ ላይ "ኢሬቻ ቱሉ" Irreecha Arfaasaa ደግሞ በተራራማ ቦታ ይከበራል። ኢሬቻ መልካ የሚከበረው በመስከረም ወር ከመስቀል በዓል በኋላ ነው። የክረምት ወራት የዝናብ፣ የደመና፣ የጭቃና የረግረግ ወቅት አልፎ ለፈካው ወራት በመምጣቱ ምስጋና የሚቀርብበት ነው። ይህ ከማህበራዊ መስተጋብር አኳያም ሰዎች የሚሰባሰቡበትና የሚገናኙበት ነው። ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ብርሃን (ብራ) ስለደረሰ ለዚያ ምልክት ይሆን ዘንድ የለመለመ እርጥብ ሣር ይዘው ወደ ወንዝ በመውረድ ንጹህ ውሃ ውስጥ እየነከሩና እየረጩ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርቡበት ነው፡፡ ኢሬቻ ቱሉ የሚከበረው የበጋው ወራት አልፎ የበልግ ዝናብ በሚጠበቅበት ወቅት ነው። በዚህም ፈጣሪ ''እርጥበት አትንፈገን፣ ወቅቶች ጊዜያቸውን ጠብቀው ይምጡ፤ የዝናብ ንፋስ ስጠን'' በማለት ለፈጣሪ ተማጽኖ የሚቀርብበት ነው። "ይህን ተራራ የፈጠርክ ፈጣሪ ወቅቱን የሰላም አድርግልን፣ የሰላም ዝናብ አዝንብልን፣ ጎርፍን ያዝልን፣ የተዘራው ፍሬ እንዲያፈራ እንለምንሃለን" እያለ በኢሬቻ ቱሉ ላይ ፈጣሪውን ይለምናል፡፡ በኢሬቻ በዓል የፈጣሪ ምህረት፣ ዕርቅ፣ አብሮነት እና በዓሉ የሰላም በዓል እንዲሆን ከላይ በተጠቀሰው መልኩ ኦሮሞ ፈጣሪውን ይጠይቃል፤ ይማፀናል፤ ለተደረገለትም ነገር ሁሉ ያመሰግናል። ኢሬቻ ምድርን እና ሰማይን ለፈጠረው "ዋቃ" "Waaqa" ምስጋናውን ለማድረስ የሚከበር ሲሆን፤ በዕድሜ ልዩነት ሳይገደብ ለዘመናት በጋራ፣ በአንድነትና በፍቅር ሲከበር ቆይቷል። በዝናባማው የክረምት ወቅት በጅረቶችና ወንዞች መሙላት ምክንያት ተራርቆ የቆየው ዘመድ አዝማድ በኢሬቻ በዓል ማክበሪያ ሥፍራ ይገናኛል፤ ይጠያየቃል፤ ናፍቆቱንም ይወጣል። አባቶች ክረምት በለሊት ይመሰላል ይላሉ። ለሊት ደግሞ ጨለማ ነው። ጨለማው ሲነጋ ደግሞ ብርሃን ነው፤ ብርሃን ደግሞ ውበት ነው፤ መታያና መድመቂያም ነው። ለዚህ ነው በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ሁሉም ውብ የባህል ልብሱን በመልበስ በደስታ በዓሉን ለማክበር የሚመጣው። ሕዝቡ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ሥፍራ የሚሄደው በተናጠል ሳይሆን በሕብረትና በአንድነት ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ የአንድነትና የአብሮነት በዓል ነው የሚባለው። ኢሬቻ የወንድማማችነትና የአንድነት አርማ ሲሆን፤ የብሩህ ዘመን ማብሰሪያ፣ የህብረ ብሔራዊ አብሮነት ማስተሳሰሪያም ጭምር ነው፡፡ በኢሬቻ ልዩነት የለም፤ ፀብ የለም፤ ክፋት የለም፤ ይልቁንም ምስጋና ይበዛል፤ ፍቅር ይሰፍናል፤ አብሮነት ያብባል፣ አንድነት ይጸናል። ኢሬቻ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው የሰላምና የአብሮነት ምልክት ነው። የኢሬቻ በዓልን ለማክበር የሚወጣው ታዳሚም እንደ እርጥብ ሣር ወይም አበባ ያለ እርጥብ ነገር በእጁ ይዞ የበዓሉን ስነ-ስርዓት ያከናውናል። ይህን የሚያደርገውም "ፈጣሪያችን ሆይ አንተ ያፀደቅከው ነው አብቦ ፍሬ ያፈራው፤ ለዚህም እናመሰግንሃለን" በማለት የፈጣሪን መልካምነት ለማሳየት ነው። በሌላ በኩል እርጥብ ሣር የልምላሜ ምልክት በመሆኑ የመልካም ምኞት መግለጫም ስለሆነም ነው በኢሬቻ በዓል እርጥብ ሣር የሚያዘው። የኢሬቻ በዓል ሲከበር ከሚከወኑ ሥርዓቶች መካከል ሴቶች ሲቄ፣ እርጥብ ሣር እንዲሁም ጮጮ ይዘው ከፊት ሲመሩ አባ ገዳዎች ደግሞ ቦኩ፣ አለንጌ እና ሌሎችንም በበዓሉ ሥርዓት የሚፈቀዱትን ሁሉ በመያዝ ወደ ሥርዓቱ አከባበር እንዲህ እያሉ ያመራሉ። ኦ ያ መሬሆ…………………መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ኡማ ሁንዳ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ ለፋ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ ያ ዋቃ መልካ ኡምቴ መሬሆ………………… ያ መሬሆ መሬሆ………………… መሬሆ እያሉ ያመራሉ። የሁሉ ፈጣሪ፣ ምድርን የፈጠርክ፣ ወንዙን የፈጠርክ . . . ምስጋና ለአንተ ይሁን በማለት ያመሰግናሉ፤ ይዘምራሉ። የኢሬቻ በዓል ሥነ-ሥርዓት በአባመልካ ተከፍቶ በአባ ገዳዎች ተመርቆ ከተጀመረ በኋላ መላው ሕዝብ በአንድነት ሥርዓቱን ያከናውናል። ኢሬቻ ሁሉም በጋራ የሚያከብረው፣ የሁሉም ማጌጫ፣ መድመቂያ እና የአብሮነት መገለጫ ነው። የበዓሉ ታዳሚዎች ከዋዜማው ጀምሮ በሆረ ፊንፊኔና በሆረ ሀርሰዲ በመሰባሰብ፤ የተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎችን በማዜምና ምስጋና በማቅረብ አድረው በነጋታው ዋናውን የምስጋና በዓልም ያከናውናሉ፡፡ የበዓሉ ታዳሚዎች የደስታና የምስጋና ምልክት የሆነውን ባህላዊ ነጫጭ ልብስ ለብሰው፣ ባህልን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ሁነቶችን በመከወን ልዩ ልዩ ዜማዎችን በማዜም፣ ግጥሞችን በማቅረብ፣ ወደ ፈጣሪ በመጸለይ እና ምስጋና በማቅረብ ሥርዓቱን ያከናውናሉ፡፡ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች የሚታወቁበትን ባህላዊ ልብስ በመልበስ በቋንቋቸው ፈጣሪን እያመሰገኑ በዓሉን በአንድነት ያከብራሉ። ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሀገር በርካታ ታዳሚዎች የሚሳተፉበት የኢሬቻ በዓል የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ከማቀራረብና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን ከመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጾኦ ያለው ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ ሀርሰዲ በዓላት ላይ ለመታደም ወደ አገር ቤት ይመጣሉ። የውጭ አገራት ጎብኚዎችና እንግዶችም በትዕይንቱ ይታደማሉ። ለአብነትም ባሳለፍነው ዓመት ከኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ አገር የመጡ ልዑካን በበዓሉ ላይ በመታደም የበዓሉን ትልቅነት እና የኢትዮጵያውያን የአብሮነት መገለጫ መሆኑን መመስከራቸው ይታወሳል። አያሌ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ያሉት ይህ የምስጋና በዓል እውነተኛ ወንድማማችነት የሚታይበት፣ አንድነት የሚጎላበት፣ አብሮነት የሚጠናከርበት፣ ሰላምና ተስፋ የሚታወጅበት አገራዊ እሴት ነው። በባህል አልባሳትና ጌጣጌጦች፣ ባህላዊ ምግቦችና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ተቋማት ኢሬቻና መሰል የአደባባይ በዓላትን እንደመልካም የገበያ አማራጭ ይጠቀሙባቸዋል። የኢሬቻ በዓል ለቱሪዝም ፍሰት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ጉልህ ነው፤ በርካታ የባህር ማዶ እና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የሚታደሙበት በዓል ነው፡፡ በዓሉ ትልቅ የቱሪዝም መስህብ ሲሆን፤ ዘርፉን በማጠናከር እና ብሔራዊ ልማትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከፍ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚናንም የሚጫወት ነው፡፡ ኢሬቻ ባህላዊ አልባሳትና ቁሳቁሶች በስፋት የሚተዋወቁበት ታላቅ መድረክ ነው። በእርግጥም ይህንን ውብ የጋራ እሴት ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ ያስፈልጋል። ኢሬቻ የምስጋና በዓል ነውና በምስጋና እንደጀመርን በምስጋናና ምርቃት እንሰነባበት። "ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ! ከመጥፎ ነገር ጠብቀን! ንጹህ ዝናብ አዝንብልን! ከእርግማን ሁሉ አርቀን! እውነትን ትቶ ከሚዋሽ አርቀን! ከረሃብ ሰውረን! ከበሽታ ሰውረን! ከጦርነት ሰውረን! ሀዬ! ሀዬ! ሀዬ!        
በትግራይ ክልል የመስቀል በዓል አከባበር
Sep 27, 2025 797
የመስቀል በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች በልዩ ድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ ነው። በዓሉ እንደየአካባቢው ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል። በትግራይ ክልልም የመስቀል በዓል እንደሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሁሉ በናፍቆት ከሚጠበቁና በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት ተርታ ይመደባል። ለዚህም ሲባል የተለያዩ ዝግጅቶች ከበዓሉ ዋዜማ በፊት እንዲጠናቀቁ የሚደረግ ሲሆን፥ በተለይ በየዓመቱ መስከረም 16 እና 17 ዘመድ አዝማድ ተጠራርተው የሚገናኙበት የፍቅርና የአብሮነት በዓል ሆኖ ይከበራል። የክርስቶስ ግማደ መስቀል በንግስት ኢሌኒ አማካኝነት መገኘቱን በማሰብ በየዓመቱ መስከረም አጋማሽ ላይ የሚከበረው የመስቀል በዓል የመስቀል ኃያልነት፣ እውነት በተደበቀበት ለዘላለም እንደማይቀርና ፍቅርን አብዝቶ የሚሰበክበት ከዚህ ባለፈም እርቅ የሚወርድበትና ደስታ የሚገለጽበት አጋጣሚ መሆኑም ይገለጻል። በትግራይ የበዓሉን ታላቅነትና ክብር ለማድመቅ ምእመናን ጽዱ ልብስ ለብሰውና የተለያዩ ዝማሬዎችን በማሰማት ደመራ ወደሚደመርበት ሥፍራ ችቦ ይዘው በመሄድ ደምራውን በማቀጣጠል የሚያከበሩት ሲሆን፣ በእለቱ የቤት እንስሳት ጭምር ቀንዳቸውና ጀርባቸው ላይ ቅቤ ተቀብተው እንዲያርፉ ይደረጋል። ዘመድ አዝማድ፣ ጎረቤታሞች፣ አብሮ አደጎችና የበዓሉ ታዳሚ እንግዶችም ተሰባስበው ማለዳ ላይ ገንፎ በማዘጋጀት ይመገባሉ። የእንስሳት እርድ በማከናወን ባህላዊ መጠጦችን በማዘጋጀት በዓሉን የፍቅር፣ የመሰባሰብ፣ የአንድነትና ተካፍሎ የመብላት በዓል መሆኑን በተግባር የሚያሳይበት ክስተት ሆኖ ያልፋል። "ዓኾይ ዓኾኾይ" የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ በማለትም ችቦ ተሎኮሶ በየቤቱ በመዞር የምረቃ እና ለሚቀጥለው ዓመትም በሰላምና ደስታ እንዲሁም እድሜና ጤናን በመመኘት ይከወናል። የአደባባይ በዓል የሆነው የመስቀል በዓል በዝማሬ፣ በሆታና እልልታ የሚገለጽ ሲሆን፤ ወርሃ መስከረም እሸት አሽቶ አበቦች አብበውና ምድር ልዩ ልምላሜን ተላብሶ የሚታይ በመሆኑ ልክ በታሪኩ እንደሰፈረው የሰላም፣ የእውነትና የአንድነት በዓል መሆኑን በተግባር የሚታይበት ነው።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም