ENA - ኢዜአ አማርኛ
አርእስተ ዜና
የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ለአገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ሚናውን ሊያጠናክር ይገባል
Aug 28, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ለአገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ሚናውን ሊያጠናክር እንደሚገባ በፓርቲው የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። የፓርቲው ሴቶች ክንፍ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዷል፡፡ ክንፉ ሴቶችን በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ መስኮች ተጠቃሚ ለማድረግ ባከናወናቸው ተግባራት፣ በተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቷል፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክንፉ እቅዶችን ወደ ተግባር የመቀየር አቅሙ እያደገ መምጣቱ ለውጤታማነቱ መሰረት ጥሏል። በኢትዮጵያ የሴቶችን ጥያቄ ጨምሮ መልስ የሚሹ መሰረታዊ ጉዳዮችን በአስተማማኝ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ ግብ መያዙን አስታውሰው፤ ግቡ እንዲሳካ የክንፉ አመራርና አባላት ድርሻ የጎላ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረትም የክንፉ ሚና የበለጠ ሊጎላ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። እስከአሁን በተከናወኑ ሥራዎች የተገኙ ስኬቶች ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ዘሃራ ዑመድ በውይይቱ ማጠቃለያ፤ የበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ የምንረባረብበት ነው ብለዋል፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዐሻራችንን ያሳረፍንበት ትልቁ ውጤታችን ነው በማለት ነው የገለጹት። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ዓለም ለመሸጋገር ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ ኢኒሼቲቩ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ሚናችንን ማጠናከር አለብን ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ጉዳይን አጀንዳ ማድረግ እና ግንዛቤ ማስፋት ላይ ይበልጥ መስራት አለብን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የክንፉ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መስከረም አበበ በበኩላቸው፤ በዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ ሴቶች የጎላ ሚና እንዲጫወቱ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በሰላም ጉዳይ ውጤት እያመጣ ያለውን የሴቶች ተሳትፎ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራ በመጥቀስ፤ ሴቶች በልማትና በፖለቲካ ተሳትፎ የተሻለ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ርብርብ እንደሚደረግም ጠቁመዋል፡፡ የክንፉ ምክትል ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፤ ክንፉ በየመስኩ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያከናወናቸው ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስገኘታቸውን አስረድተዋል፡፡ የውጤቱን አፈጻጸም ወጥ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም በቅንጅት የመስራት ጉዳይ ትኩረት እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡ በውይይቱ ማጠቃለያም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የክንፉ የክልልና ከተማ መስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እውቅና ተሰጥቷል።
በቀላሉ ማግኘት እየተቻለ ችላ የሚባለው ቫይታሚን ዲ
Aug 28, 2025 43
የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የቫይታሚን ዲ እጥረት ለተለያዩ በሽታዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ገልጸዋል። የቫይታሚን ዲ እጥረት የሚያስከትው ጉዳት፣ ለቫይታሚን ዲ እጥረት አጋላጭ ምክንያቶች፣ በቫይታሚን ዲ እጥረት ላለመያዝ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች ባለሙያው ከታች በቀረበው መሠረት አብራርተዋል። • የቫይታሚን ዲ እጥረት የሚያስከትው ጉዳት O በልጆች እና ዐዋቂዎች የአጥንት ጤናማነት ላይ ጉዳት ያደርሳል። O የጡንቻዎች ድክመት ብሎም ህመም ሊከሰት ይችላል። O ድካም፣ የነርቭ ሥርዓት ህመም፣ የመንፈስ ጭንቀት ያጋጥማል። O የበሽታ መከላከያ ሥርዓትን በማዳከም ለበሽታዎች የመጋለጥ ዕድልን ይጨምራል። • አጋላጭ ምክንያቶች O በቂ ቀጥተኛ የሆነ የፀሐይ ብርሃን አለማግኘት፤ O ከምግብ በበቂ ሁኔታ ቫይታሚን ዲ አለማግኘት፤ O ጠቆር ያለ የቆዳ ቀለም (ተፈጥሯዊ አጋላጭ ምክንያት ነው)፤ O አለባባስ (ሙሉ ሰውነትን ከፀሐይ በሚከልል መልኩ መልበስ)፤ O በሽታዎች (እንደ ጉበት፣ ኩላሊት ያሉ ህመሞች ከምግብም ሆነ ከፀሐይ የምናገኘውን ቫይታሚን ዲ ሰውነታችን እንዲጠቀምበት ለመለወጥ በሚደረግ ሂደት ላይ ተጽዕኖ ያሳድራሉ)። O ውፍረት (በስብ ውስጥ የቫይታሚን ዲ መከማቸት)፤ O መድኃኒቶች (ለምሳሌ የአንቲሴዘር፣ የቲቢ፣ ስቴሮኢድስ፣ የአንጀት እንቅሰቃሴን የሚጨምሩ፣ የሃሞት ፈሳሽን ከሰውነት የሚያወጡ መድኃኒቶች)፤ • በበቫይታሚን ዲ እጥረት ላለመያዝ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ 👉 ደኅንነቱ የተጠበቀ የፀሐይ መጋለጥ (እንደ ቆዳ ዓይነት የሚወሰን ሆኖ በሣምንት ለጥቂት ጊዜያት በየቀኑ ከ10 እስከ 15 ደቂቃዎች)፤ 👉 በቫይታሚን ዲ የበለጸጉ ምግቦች (ሳልሞን፣ ሰርዲን፣ ወተት፣ ጥራጥሬ፣ የእንቁላል አስኳሎች፣ ጉበት) መመገብ፤ 👉 ከምግብ እና ከፀሐይ ብርሃን የሚገኘው የቫይታሚን ዲ በቂ ካልሆነ ተጨማሪ ቪታሚን ዲ መውሰድ፤ 👉 ከፍተኛ ተጋላጭነት ላለባቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች (አረጋውያን፣ ጽኑ ህሙማን፣ ማላብሶርፕሽን ላለባቸው ሰዎች፣ በከተሞች አካባቢ ጥቁር ቆዳ ላለባቸው ሰዎች) ምርመራ ማድረግ፤ 👉 ከቤት ውጭ የሚደረግ እንቅስቃሴ (ከቤት ውጭ በተለይም ለልጆች እና ለአረጋውያን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጊዜን ማበረታታት)፤ 👉 ክብደትን መቆጣጠር (ከመጠን ያለፈ ውፍረት ከዝቅተኛ የቫይታሚን ዲ ጋር የተያያዘ ነው)፤ 👉 የአካል ብቃት እንቅስቃሴ (የአጥንት እና የጡንቻን ጤና ያሻሽላል፣ ከቫይታሚን ዲ ጋር በመተባበር ይሠራል)፤ • የቫይታሚን ዲ እጥረት ያለባቸው ሰዎች ምን አይነት ጥቃቄ እንዲያደርጉ ይመከራል? በአብዛኛው በከተማ የሚኖሩ ሰዎች ለቫይታሚን ዲ እጥረት ተጋላጭ መሆናቸውን ያነሱት ዶክተር ፍፁም፤ ለምሳሌ በመካከለኛ የትምህርት ዕድሜ ያሉ ልጆች በከተማ 61 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም በገጠር 21 ነጥብ 2 በመቶ የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባችው የጥናት ውጤት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። የቫይታሚን ዲ እጥረትን ለማስተካከል በግል ከሚደረጉ ጥረቶች ባለፈ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድ በቃላሉ ማከም እንደሚቻልም ነው ያስገነዘቡት። በተለይም ለዚህ ችግር ተጋላጭ የሆኑ ማለትም የጉበት እና የኩላሊት እንዲሁም የማልአብዞርብሽን ችግር ያለባቸው ብሎም በክረምት ወቅት የተወለዱ ልጆች (በቂ የፀሐይ ብርሃን ስለማያገኙ ) የመድሃኒት ድጋፍ መውሰድ ይኖርባቸዋል ብለዋል።
የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ድልድል ይፋ ሆነ
Aug 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የ2025/26 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ድልድል ዛሬ ማምሻውን በሞናኮ ይፋ ሆኗል። ውድድሩ መስከረም 6 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ከባለፈው የውድድር ዓመት አንስቶ ሻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ድልድል ፎርማትን በማስቀረት 36 ክለቦች በ4 ቋቶች (Pots) በመከፋፈል እንዲጫወቱ የሚያደርግ አዲስ አሰራር መተግበር መጀመሩ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት 36ቱ ቡድኖች በ4 ቋቶች የተደለደሉ ሲሆን በእያንዳንዱ ቋት 9 ክለቦች ይገኛሉ። በቋት አንድ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒኤስጂ፣ ሪያል ማድሪድ፣ ማንችስተር ሲቲ፣ ባየር ሙኒክ፣ ሊቨርፑል፣ ኢንተር ሚላን፣ ቼልሲ፣ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ እና ባርሴሎና ተደልድለዋል። አርሰናል፣ ባየር ሌቨርኩሰን፣ አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ቤኔፊካ፣ አትላንታ፣ ቪያሪያል፣ ጁቬንቱስ፣ ኢንትራክት ፍራንክፈርት እና ክለብ ብሩዥ በቋት ሁለት የሚገኙ ናቸው። በቋት ሶስት ቶተንሃም ሆትስፐርስ፣ ፒኤስቪ አይንድሆቨን፣ አያክስ፣ ናፖሊ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን፣ ኦሎምፒያኮስ፣ ስላቪያ ፕራግ፣ ቦዶ ግሊምት እና ማርሴይ ተገናኝተዋል። ኮፐንሃገን፣ ሞናኮ፣ ጋለታሳራይ፣ ሴንት ዩኒየን ጊሎስ፣ ካራባግ፣ አትሌቲኮ ቢልባኦ፣ ኒውካስትል ዩናይትድ፣ ፓፎስ እና ካይራት አልማቲ በቋት አራት የተደለደሉ ክለቦች ናቸው። አንድ ክለብ በራሱ ቋት ካለ ሁለት ቡድንና በእያንዳንዱ ቋት ካሉ ሁለት ክለቦች ጋር ጨዋታውን ያደርጋል። በዚህም አንድ ክለብ ስምንት ጨዋታ ያደርጋል። ከ36 ክለቦች መካከል በስምንት ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ስምንት ቡድኖች በቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፉ ይገባሉ። ቀሪዎቹ ስምንት ወደ ጥሎ ማለፉ የሚገቡ ቡድኖች በሁለት የማጣሪያ ዙሮች ተጫውተው 16ት ውስጥ ይገባሉ። ከጥሎ ማለፉ አንስቶ ያለው የውድድር ፎርማት ከዚህ ቀደም ከነበረው ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው። ከዚህ ቀደም በውድድሩ ላይ ይሳተፉ የነበሩ 32 ክለቦች በአሁኑ የውድድር አሰራር ወደ 36 ከፍ ማለታቸው ይታወቃል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል
Aug 28, 2025 54
ሆሳዕና፤ ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ወደሥራ መገባቱን የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምና የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በሆሳዕና ከተማ መክሯል፡፡ በዚህ ወቅት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ እንደገለጹት በተጠናቀቀው የሥራ ዘመን የክልሉን ፀጋ መሰረት ያደረጉ አማራጮችን በመጠቀም የወጣቶችን የሥራ አጥነት ችግር ለማቃለል ሥራዎች ተከናውነዋል። ይህም ኢንተርፕራይዞችን በክህሎት ስልጠና ከመደገፍ ጀምሮ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ በመስሪያና በመሸጫ ቦታ ዝግጅት፣ በብድር አቅርቦትና ተወዳዳሪ ማድረግ ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ለ371 ሺህ 351 ወጣቶች የሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከታቀደው በላይ ማከናወን መቻሉን አውስተዋል፡፡ በተያዘው የበጀት ዓመትም ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ለማድረግ ወደ ተግባር መገባቱን ነው ያመለከቱት። የሀድያ ዞን ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ሊረንሶ በበኩላቸው፤ በዞኑ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ምቹ መደላድል እየተፈጠረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በዚህም በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ የሥራ አማራጮችን በመለየት ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ወደ ተግባራዊ ሥራ ተገብቷል ብለዋል፡፡ በ2017 በጀት ዓመት ከ45 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩን የገለጹት ደግሞ የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጁ ነስሩ ናቸው። በተያዘው በጀት ዓመትም ካለፈው የሥራ ዘመን ተሞክሮ በመውሰድ የወጣቱን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማስፋት ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ በእንጨትና የብረታ ብረት ማምረቻ ስራ ላይ የተሰማራው ወጣት ሄኖክ አንጁሎ፤ ዘንድሮ በተፈጠረለት የሥራ ዕድል ገቢ እያገኘ እራሱንና ቤተሰቡን በማስተዳደር ተጠቃሚ መሆኑን አመልክቷል። በምክክር መድረኩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆን ይገባዋል
Aug 28, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆን እንደሚገባው የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ ገለጹ፡፡ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወሳል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አዋጁ ተግባራዊ በሚሆንበት አግባብ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ሰጥቷል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ እንዳሉትም፤ አዋጁ ከያዛቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል የፕላስቲክ ቆሻሻ አያያዝና የአወጋገድ ስርዓት ይገኝበታል፡፡ የፕላስቲክ ውጤቶች በመሬት ውስጥ ሳይበሰብሱ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ በመሆናቸው ለአካባቢ ብክለት መንስዔ፣ ለሰው ልጅ ጤና ደግሞ ጉዳት እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የሚጣጣም እና ዘመኑን የሚዋጅ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ማዘጋጀቷን ጠቁመዋል። በአዋጁ መሠረት ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት፣ ማምረትና ለገበያ ማቅረብ እንደማይቻል አመልክተዋል። ይህም ከስድስት ወራት በኋላ በመላው ሀገሪቷ ተፈጻሚ እንደሚሆን ተናግረዋል። በአካባቢም ሆነ በሰዎች ጤና ላይ ጉዳት የማያደርሱ ምርቶችን ለማቅረብ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የዛሬው ስልጠናም አዋጁ በአግባቡ እንዲፈጸም ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ እንዲይዙ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የከተማ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ክትትል ዴስክ ሃላፊ ዋሲሁን አለሙ፤ ጽዱና ለኑሮ ምቹ አካባቢ ለመፍጠር እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ የፕላስቲክ ቆሻሻ አያያዝና የአወጋገድ ስርዓት ዙሪያ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቂ ግንዛቤ በመያዝ የበኩላቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ተስፋዬ ደጀኔ፤ ስልጠናው አዋጁን ተፈጻሚ ለማድረግ የጋራ አቋምና አቅም እንድንይዝ የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡
ፖለቲካ
የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ለአገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ሚናውን ሊያጠናክር ይገባል
Aug 28, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ለአገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ሚናውን ሊያጠናክር እንደሚገባ በፓርቲው የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። የፓርቲው ሴቶች ክንፍ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዷል፡፡ ክንፉ ሴቶችን በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ መስኮች ተጠቃሚ ለማድረግ ባከናወናቸው ተግባራት፣ በተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቷል፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክንፉ እቅዶችን ወደ ተግባር የመቀየር አቅሙ እያደገ መምጣቱ ለውጤታማነቱ መሰረት ጥሏል። በኢትዮጵያ የሴቶችን ጥያቄ ጨምሮ መልስ የሚሹ መሰረታዊ ጉዳዮችን በአስተማማኝ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ ግብ መያዙን አስታውሰው፤ ግቡ እንዲሳካ የክንፉ አመራርና አባላት ድርሻ የጎላ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረትም የክንፉ ሚና የበለጠ ሊጎላ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። እስከአሁን በተከናወኑ ሥራዎች የተገኙ ስኬቶች ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ዘሃራ ዑመድ በውይይቱ ማጠቃለያ፤ የበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ የምንረባረብበት ነው ብለዋል፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዐሻራችንን ያሳረፍንበት ትልቁ ውጤታችን ነው በማለት ነው የገለጹት። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ዓለም ለመሸጋገር ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ ኢኒሼቲቩ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ሚናችንን ማጠናከር አለብን ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ጉዳይን አጀንዳ ማድረግ እና ግንዛቤ ማስፋት ላይ ይበልጥ መስራት አለብን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የክንፉ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መስከረም አበበ በበኩላቸው፤ በዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ ሴቶች የጎላ ሚና እንዲጫወቱ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በሰላም ጉዳይ ውጤት እያመጣ ያለውን የሴቶች ተሳትፎ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራ በመጥቀስ፤ ሴቶች በልማትና በፖለቲካ ተሳትፎ የተሻለ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ርብርብ እንደሚደረግም ጠቁመዋል፡፡ የክንፉ ምክትል ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፤ ክንፉ በየመስኩ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያከናወናቸው ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስገኘታቸውን አስረድተዋል፡፡ የውጤቱን አፈጻጸም ወጥ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም በቅንጅት የመስራት ጉዳይ ትኩረት እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡ በውይይቱ ማጠቃለያም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የክንፉ የክልልና ከተማ መስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እውቅና ተሰጥቷል።
የቦትስዋና ምክትል ፕሬዝዳንት አዲስ አበባ ገቡ
Aug 28, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ የቦትስዋና ምክትል ፕሬዝዳንት ንዳባ ኒኮዚናቲ ጋዖላቲ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ ቦሌ አለማቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በአዲስ አበባ ቆይታቸውም በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ የማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን የሚኒስትሮች ጉባዔ ላይ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የተጀመሩ አገራዊ ውጥኖች ከዳር እንዲደርሱ መረባረብ ይገባል
Aug 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የተጀመሩ አገራዊ ውጥኖች ከዳር እንዲደርሱ ልንረባረብ ይገባል ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፕሬዝዳንት ዘሃራ ዑመድ ገለጹ፡፡ የፓርቲው ሴቶች ክንፍ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዷል፡፡ ክንፉ ሴቶችን በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ መስኮች ተጠቃሚ ለማድረግ ባከናወናቸው ተግባራት፣ በተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቷል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ዘሃራ ዑመድ በውይይቱ ማጠቃለያ የበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ የምንረባረብበት ነው ብለዋል፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዐሻራችንን ያሳረፍንበት ትልቁ ውጤታችን ነው ብለዋል። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ዓለም ለመሸጋገር ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ ኢኒሼቲቩ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ሚናችንን ማጠናከር አለብን ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ጉዳይን አጀንዳ ማድረግ እና ግንዛቤ ማስፋት ላይ ይበልጥ መስራት አለብን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የክንፉ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መስከረም አበበ በበኩላቸው፤ በዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ ሴቶች የጎላ ሚና እንዲጫወቱ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በሰላም ጉዳይ ውጤት እያመጣ ያለውን የሴቶች ተሳትፎ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራ በመጥቀስ ሴቶች በልማትና በፖለቲካ ተሳትፎ የተሻለ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ርብርብ እንደሚደረግም ጠቁመዋል፡፡ የክንፉ ምክትል ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፤ ክንፉ በየመስኩ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያከናወናቸው ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስገኘታቸውን አስረድተዋል፡፡ የውጤቱን አፈጻጸም ወጥ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም በቅንጅት የመስራት ጉዳይ ትኩረት እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡
የቀድሞ ታጣቂዎች ማህበረሰቡን በልማት ለመካስ መዘጋጀት አለባቸው - አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Aug 28, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ የቀድሞ ታጣቂዎች ማህበረሰቡን በዘላቂ የሰላም ግንባታ እና በልማት ለመካስ ሊዘጋጁ እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የቀድሞ ታጣቂዎችን በደብረ ብርሐን ጊዜያዊ የዲሞብላይዜሽን ማዕከል በተሀድሶ ስልጠና መልሶ የማቋቋም ስልጠና መሰጠት ጀምሯል። በተሀድሶ ስልጠና ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች፣ የፌደራልና የክልል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል። በሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፥ የክልሉ መንግሥት ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። የትኛውም ችግርና የሀሳብ ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የሰላም አማራጭን በመከተል በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ እያቀረበ መሆኑንም ገልጸዋል። ሆኖም ጽንፈኛው ቡድን ፖለቲካዊ ፍላጎቱን በኃይል ለማሳካት በፈጠረው ችግር በህዝብ ላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ማድረሱን አውስተዋል። በሌላ በኩል የኃይል አካሄድ ህዝብን ከመጉዳት ያለፈ ዓላማ እንደሌለው የተረዱና ለሰላም ቅድሚያ የሰጡ በርካታ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ተሃድሶ ስልጠና እየገቡ መሆኑን ተናግረዋል። የቀድሞ ታጣቂዎቹ ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ ነው ያሉት ዶክተር አሕመዲን፥ ለህዝብ አብሮነት፣ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ግንባታ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በጫካ የሚገኘው ጽንፈኛ ኃይል ከዚህ ቀደም የአማራን ህዝብ የሽምግልና እሴት በሚንድ መልኩ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሴቶችና ህፃናት ላይ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት መፈጸሙን ገልጸዋል። እንዲህ ያለው የጽንፈኝነት አስተሳሰብ ከሞራል ፍጹም ያፈነገጠና የሚያደርሰው ማህበራዊና ሰብዓዊ ጉዳትም ከፍተኛ በመሆኑ ሁሉም ሊቃወመውና እንዳይደገም ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። የክልሉ መንግስት ህዝብን ከድህነት ወደ ተሟላ ብልፅግና የሚያሸጋግር የአምስት ዓመት የልማት ዕቅድ በመቅረጽ እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል። ለስኬቱም ህዝቡ፣ የቀድሞ ታጣቂዎችና ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል
Aug 28, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ በተለያዩ የስራ መስኮች ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አስታወቀ። የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ውይይት እያካሄደ ነው፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ዋና ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ መዓዛ ካሚቶ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ መስኮች የሴቶችን ተጠቃሚነት ያጎሉ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከስራ ዕድል ፈጠራ እና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ዙሪያ የሴቶችን ግንዛቤ በማሳደግ በመርሃ ግብሩ እንዲሳተፉ የሚያስችሉ አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል፡፡ ለአብነትም በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አምስት ሚሊዮን ሴቶችን ለማሳተፍ ግብ መያዙን አስታውሰው፤ አምስት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ሴቶች በመርሃ ግብሩ እንዲሳተፉ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ በአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ እና እድሳት፣ በማዕድ ማጋራት፣ በደም ልገሳ እንዲሁም በጎ ፈቃድ ስራዎች የጎላ ተሳትፎ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል ፡፡ እንደ ወይዘሮ መዓዛ ገለጻ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ክንፉ ለሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል ፡፡ በዘላቂ ሰላም ግንባታና በአገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ሴቶችን በማሳተፍ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከአባላቱ በንቅናቄ ከ185 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡንም ለአብነት አንስተዋል ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የክንፉ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መስከረም አበበ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በቀጣይ የሴቶችን አቅም በማሳደግ የፖለቲካ ተሳትፏቸውን የማሳደግ ስራ በትኩረት ይከናወናል፡፡ ቀጣዩ ምርጫ ሰላማዊ እና ዲሞክራሲያ በሆነ መንገድ እንዲከናወን በሚደረገው ጥረት የሴቶች ሚና ትልቅ ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቷ፤ በቀጣዩ ምርጫ ሴቶች የጎላ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ይሰራል ብለዋል፡፡
መንግሥት በተሀድሶ ስልጠና የሚያልፉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማትና የሰላም ግንባታ አካል እንዲሆኑ በትኩረት እየሰራ ነው
Aug 28, 2025 134
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ መንግሥት በተሀድሶ ስልጠና የሚያልፉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማትና የሰላም ግንባታ አካል እንዲሆኑ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች በተሀድሶ ስልጠና በማሳለፍ ወደ ማህበረሰባቸው እንዲቀላቀሉ መደረጉን አስታውቀዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በደብረ ብርሐን ጊዜያዊ የዲሞብላይዜሽን ማዕከል በተሀድሶ ስልጠና መልሶ የማቋቋም ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ መንግስት ምንጊዜም ሰላምን ለማጽናት ዝግጁ ነው። ለዚህም የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማህብረሰቡ እንዲቀላቀሉ እንዲሁም የልማትና የሰላም ኃይል እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። በአማራ ክልልም በተለያዩ የተሀድሶ ማዕከላት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና በማሳለፍ መደበኛ ህይወታቸውን እንዲመሩ መንግሥት ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል። በተሀድሶ ስልጠና የሚያልፉ የቀድሞ ታጣቂዎችም በቀጣይ ህይወታቸው ህዝብና ሀገራቸውን መካስ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በተሳሳተ መንገድ በጫካ የሚገኙ የታጠቁ አካላት የመንግስትን ጽኑ የሰላም ፍላጎት በመቀበል ወደሰላም እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ72 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች በተሀድሶ ስልጠና አልፈው ወደ ማህበረሰባቸው እንዲቀላቀሉ መደረጉን ገልጸዋል። የተሀድሶ ስልጠናው ለልማትና ለሰላም ግንባታ አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአማራ ክልል በ2ኛው ዙር በደብረ ብርሐን፣ በኮምቦልቻና ጎንደር ጊዜያዊ የተሀድሶ ማዕከላት ከ6 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ተሃድሶ ስልጠና መግባታቸውን ተናግረዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም አምባሳደሮች እንደሆኑም አንስተዋል። በተሀድሶ ስልጠና ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የጸጥታ ተቋማት አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን የአየር ኃይል ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Aug 28, 2025 115
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን በሁለቱ ሀገራት አየር ኃይሎች መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ከፓኪስታን የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ኤር ቺፍ ማርሻል ዛሂር አህመድ ባበር ሲዱ ጋር በኢስላም አባድ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የመከላከያ ሠራዊትን በዘመናዊ መልክ ለማዋቀር ስልታዊ ትኩረትን ጨምሮ ኢትዮጵያ በሁለንተናዊ የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል። የፓኪስታን አየር ኃይል ያለውን ጠንካራ የተግባር ዝግጁነት፣ እያደገ የመጣውን ሁለገብ ዘርፍ ችሎታዎች እና አስተማማኝ የመከላከል አቋም አድንቀዋል። ኤር ቺፍ ማርሻል ዛሂር አህመድ ባበር ሲዱ በበኩላቸው፤ ጉብኝቱ በሀገራቱ መካከል እያደገ የመጣውን ግንኙነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። ፓኪስታን ከኢትዮጵያ ጋር ላላት ግንኙነት ከፍተኛ ዋጋ እንደምትሰጥ ጠቅሰው፤ የሀገራቸው አየር ኃይል በአቅም ግንባታ፣ በላቀ ስልጠና እና በክንውን ዘርፎች ለኢትዮጵያ አየር ኃይል ድጋፍ ለማድረግ ጽኑ አቋም እንዳለው አረጋግጠዋል። በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ጉብኝቱ በሁለቱ ወዳጅ ሀገራት አየር ኃይሎች መካከል ለአዲስ ስልታዊ የትብብር ምዕራፍ ጠንካራ መሰረት መጣሉን ገልፀዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች ይጠናከራሉ - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Aug 27, 2025 193
ሆሳዕና ፤ነሐሴ 21/2017 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ "ሰላምን ማፅናት ለክልሉ ሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ዘላቂ ሰላምን በማጽናት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡ ለዚህም የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ትግበራን የማስፋትና የተጠናከረ የህግ ማስከበር ስራ ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል፡፡ ሰላምን ማስጠበቅና ማፅናት በክልሉ እየተመዘገበ ያለውን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ የሀይማኖት ተቋማት፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የትምህርት ተቋማት በሰላም ግንባታ ላይ አበክረው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በዚህም በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምን በማፅናት የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በበኩላቸው በክልሉ የፀጥታ መዋቅሩ ከህዝቡ ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሰላምን በዘላቂነት ለማጽናት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል፡፡ የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት አባል ወይዘሮ ጀሚላ ኢብራሂም፣ የሴቶችን አደረጃጀት በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥና እድገትን ለማስቀጠል መስራት ይገባል ብለዋል። ሌላው የምክር ቤቱ አባል ወጣት ነስሩ ኡመር በበኩሉ በአካባቢው የህዝብ ለህዝብ ትስስር በማጠናከር ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየሰራን ነው ብሏል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን አስተዳዳሪዎች፣ የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አባላት፣ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግዎች ተሳትፈዋል፡፡
ፖለቲካ
የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ለአገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ሚናውን ሊያጠናክር ይገባል
Aug 28, 2025 57
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ለአገረ መንግሥት ግንባታ ስኬት ሚናውን ሊያጠናክር እንደሚገባ በፓርቲው የዲሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙ ገለጹ። የፓርቲው ሴቶች ክንፍ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዷል፡፡ ክንፉ ሴቶችን በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ መስኮች ተጠቃሚ ለማድረግ ባከናወናቸው ተግባራት፣ በተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቷል፡፡ በብልፅግና ፓርቲ የዋና ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ መለሰ ዓለሙ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ክንፉ እቅዶችን ወደ ተግባር የመቀየር አቅሙ እያደገ መምጣቱ ለውጤታማነቱ መሰረት ጥሏል። በኢትዮጵያ የሴቶችን ጥያቄ ጨምሮ መልስ የሚሹ መሰረታዊ ጉዳዮችን በአስተማማኝ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ ግብ መያዙን አስታውሰው፤ ግቡ እንዲሳካ የክንፉ አመራርና አባላት ድርሻ የጎላ ሊሆን ይገባል ብለዋል። ጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረትም የክንፉ ሚና የበለጠ ሊጎላ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል። እስከአሁን በተከናወኑ ሥራዎች የተገኙ ስኬቶች ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መሥራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል። የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ዘሃራ ዑመድ በውይይቱ ማጠቃለያ፤ የበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ የምንረባረብበት ነው ብለዋል፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዐሻራችንን ያሳረፍንበት ትልቁ ውጤታችን ነው በማለት ነው የገለጹት። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ዓለም ለመሸጋገር ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ ኢኒሼቲቩ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ሚናችንን ማጠናከር አለብን ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ጉዳይን አጀንዳ ማድረግ እና ግንዛቤ ማስፋት ላይ ይበልጥ መስራት አለብን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የክንፉ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መስከረም አበበ በበኩላቸው፤ በዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ ሴቶች የጎላ ሚና እንዲጫወቱ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በሰላም ጉዳይ ውጤት እያመጣ ያለውን የሴቶች ተሳትፎ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራ በመጥቀስ፤ ሴቶች በልማትና በፖለቲካ ተሳትፎ የተሻለ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ርብርብ እንደሚደረግም ጠቁመዋል፡፡ የክንፉ ምክትል ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፤ ክንፉ በየመስኩ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያከናወናቸው ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስገኘታቸውን አስረድተዋል፡፡ የውጤቱን አፈጻጸም ወጥ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም በቅንጅት የመስራት ጉዳይ ትኩረት እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡ በውይይቱ ማጠቃለያም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የክንፉ የክልልና ከተማ መስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እውቅና ተሰጥቷል።
የቦትስዋና ምክትል ፕሬዝዳንት አዲስ አበባ ገቡ
Aug 28, 2025 68
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ የቦትስዋና ምክትል ፕሬዝዳንት ንዳባ ኒኮዚናቲ ጋዖላቲ ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ ቦሌ አለማቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በአዲስ አበባ ቆይታቸውም በወንጀል ድርጊት የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ የማቅረብ ወንጀል መከላከል ቡድን የሚኒስትሮች ጉባዔ ላይ እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የተጀመሩ አገራዊ ውጥኖች ከዳር እንዲደርሱ መረባረብ ይገባል
Aug 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የተጀመሩ አገራዊ ውጥኖች ከዳር እንዲደርሱ ልንረባረብ ይገባል ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፕሬዝዳንት ዘሃራ ዑመድ ገለጹ፡፡ የፓርቲው ሴቶች ክንፍ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዷል፡፡ ክንፉ ሴቶችን በማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚና ፖለቲካ መስኮች ተጠቃሚ ለማድረግ ባከናወናቸው ተግባራት፣ በተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ተወያይቷል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ዘሃራ ዑመድ በውይይቱ ማጠቃለያ የበጀት ዓመቱ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ የምንረባረብበት ነው ብለዋል፡፡ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዐሻራችንን ያሳረፍንበት ትልቁ ውጤታችን ነው ብለዋል። የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ዓለም ለመሸጋገር ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ ኢኒሼቲቩ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ሚናችንን ማጠናከር አለብን ብለዋል፡፡ የብሔራዊ መታወቂያ ጉዳይን አጀንዳ ማድረግ እና ግንዛቤ ማስፋት ላይ ይበልጥ መስራት አለብን ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንትና የክንፉ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መስከረም አበበ በበኩላቸው፤ በዘላቂ ሰላም ግንባታ ላይ ሴቶች የጎላ ሚና እንዲጫወቱ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ በሰላም ጉዳይ ውጤት እያመጣ ያለውን የሴቶች ተሳትፎ ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚሰራ በመጥቀስ ሴቶች በልማትና በፖለቲካ ተሳትፎ የተሻለ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ርብርብ እንደሚደረግም ጠቁመዋል፡፡ የክንፉ ምክትል ፕሬዝዳንት ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፤ ክንፉ በየመስኩ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያከናወናቸው ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማስገኘታቸውን አስረድተዋል፡፡ የውጤቱን አፈጻጸም ወጥ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም በቅንጅት የመስራት ጉዳይ ትኩረት እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡
የቀድሞ ታጣቂዎች ማህበረሰቡን በልማት ለመካስ መዘጋጀት አለባቸው - አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)
Aug 28, 2025 95
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ የቀድሞ ታጣቂዎች ማህበረሰቡን በዘላቂ የሰላም ግንባታ እና በልማት ለመካስ ሊዘጋጁ እንደሚገባ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የቀድሞ ታጣቂዎችን በደብረ ብርሐን ጊዜያዊ የዲሞብላይዜሽን ማዕከል በተሀድሶ ስልጠና መልሶ የማቋቋም ስልጠና መሰጠት ጀምሯል። በተሀድሶ ስልጠና ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች፣ የፌደራልና የክልል መንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል። በሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፥ የክልሉ መንግሥት ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል። የትኛውም ችግርና የሀሳብ ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የሰላም አማራጭን በመከተል በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ እያቀረበ መሆኑንም ገልጸዋል። ሆኖም ጽንፈኛው ቡድን ፖለቲካዊ ፍላጎቱን በኃይል ለማሳካት በፈጠረው ችግር በህዝብ ላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ማድረሱን አውስተዋል። በሌላ በኩል የኃይል አካሄድ ህዝብን ከመጉዳት ያለፈ ዓላማ እንደሌለው የተረዱና ለሰላም ቅድሚያ የሰጡ በርካታ ታጣቂዎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ተሃድሶ ስልጠና እየገቡ መሆኑን ተናግረዋል። የቀድሞ ታጣቂዎቹ ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ እየተቀላቀሉ ነው ያሉት ዶክተር አሕመዲን፥ ለህዝብ አብሮነት፣ ለዘላቂ ሰላምና ልማት ግንባታ በቁርጠኝነት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል። በጫካ የሚገኘው ጽንፈኛ ኃይል ከዚህ ቀደም የአማራን ህዝብ የሽምግልና እሴት በሚንድ መልኩ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሴቶችና ህፃናት ላይ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት መፈጸሙን ገልጸዋል። እንዲህ ያለው የጽንፈኝነት አስተሳሰብ ከሞራል ፍጹም ያፈነገጠና የሚያደርሰው ማህበራዊና ሰብዓዊ ጉዳትም ከፍተኛ በመሆኑ ሁሉም ሊቃወመውና እንዳይደገም ሊያደርግ ይገባል ብለዋል። የክልሉ መንግስት ህዝብን ከድህነት ወደ ተሟላ ብልፅግና የሚያሸጋግር የአምስት ዓመት የልማት ዕቅድ በመቅረጽ እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል። ለስኬቱም ህዝቡ፣ የቀድሞ ታጣቂዎችና ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል
Aug 28, 2025 87
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ በተለያዩ የስራ መስኮች ሴቶችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አስታወቀ። የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ውይይት እያካሄደ ነው፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ዋና ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ መዓዛ ካሚቶ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ መስኮች የሴቶችን ተጠቃሚነት ያጎሉ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከስራ ዕድል ፈጠራ እና በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ዙሪያ የሴቶችን ግንዛቤ በማሳደግ በመርሃ ግብሩ እንዲሳተፉ የሚያስችሉ አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል፡፡ ለአብነትም በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አምስት ሚሊዮን ሴቶችን ለማሳተፍ ግብ መያዙን አስታውሰው፤ አምስት ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ሴቶች በመርሃ ግብሩ እንዲሳተፉ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ በአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ እና እድሳት፣ በማዕድ ማጋራት፣ በደም ልገሳ እንዲሁም በጎ ፈቃድ ስራዎች የጎላ ተሳትፎ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል ፡፡ እንደ ወይዘሮ መዓዛ ገለጻ፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ክንፉ ለሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል ፡፡ በዘላቂ ሰላም ግንባታና በአገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ሴቶችን በማሳተፍ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከአባላቱ በንቅናቄ ከ185 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡንም ለአብነት አንስተዋል ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዝዳንት እና የክንፉ ዋና ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መስከረም አበበ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በቀጣይ የሴቶችን አቅም በማሳደግ የፖለቲካ ተሳትፏቸውን የማሳደግ ስራ በትኩረት ይከናወናል፡፡ ቀጣዩ ምርጫ ሰላማዊ እና ዲሞክራሲያ በሆነ መንገድ እንዲከናወን በሚደረገው ጥረት የሴቶች ሚና ትልቅ ነው ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቷ፤ በቀጣዩ ምርጫ ሴቶች የጎላ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ይሰራል ብለዋል፡፡
መንግሥት በተሀድሶ ስልጠና የሚያልፉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማትና የሰላም ግንባታ አካል እንዲሆኑ በትኩረት እየሰራ ነው
Aug 28, 2025 134
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ መንግሥት በተሀድሶ ስልጠና የሚያልፉ የቀድሞ ታጣቂዎች የልማትና የሰላም ግንባታ አካል እንዲሆኑ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ በርካታ የቀድሞ ታጣቂዎች በተሀድሶ ስልጠና በማሳለፍ ወደ ማህበረሰባቸው እንዲቀላቀሉ መደረጉን አስታውቀዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎችን በደብረ ብርሐን ጊዜያዊ የዲሞብላይዜሽን ማዕከል በተሀድሶ ስልጠና መልሶ የማቋቋም ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፥ መንግስት ምንጊዜም ሰላምን ለማጽናት ዝግጁ ነው። ለዚህም የቀድሞ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማህብረሰቡ እንዲቀላቀሉ እንዲሁም የልማትና የሰላም ኃይል እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል። በአማራ ክልልም በተለያዩ የተሀድሶ ማዕከላት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የቀድሞ ታጣቂዎችን በተሀድሶ ስልጠና በማሳለፍ መደበኛ ህይወታቸውን እንዲመሩ መንግሥት ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል። በተሀድሶ ስልጠና የሚያልፉ የቀድሞ ታጣቂዎችም በቀጣይ ህይወታቸው ህዝብና ሀገራቸውን መካስ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል። በተሳሳተ መንገድ በጫካ የሚገኙ የታጠቁ አካላት የመንግስትን ጽኑ የሰላም ፍላጎት በመቀበል ወደሰላም እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል። የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ72 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች በተሀድሶ ስልጠና አልፈው ወደ ማህበረሰባቸው እንዲቀላቀሉ መደረጉን ገልጸዋል። የተሀድሶ ስልጠናው ለልማትና ለሰላም ግንባታ አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። በአማራ ክልል በ2ኛው ዙር በደብረ ብርሐን፣ በኮምቦልቻና ጎንደር ጊዜያዊ የተሀድሶ ማዕከላት ከ6 ሺህ በላይ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ተሃድሶ ስልጠና መግባታቸውን ተናግረዋል። የመንግስትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የቀድሞ ታጣቂዎች የሰላም አምባሳደሮች እንደሆኑም አንስተዋል። በተሀድሶ ስልጠና ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የጸጥታ ተቋማት አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።
ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን የአየር ኃይል ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
Aug 28, 2025 115
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን በሁለቱ ሀገራት አየር ኃይሎች መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ትብብር ለማጠናከር ተስማምተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ከፓኪስታን የአየር ኃይል ዋና አዛዥ ኤር ቺፍ ማርሻል ዛሂር አህመድ ባበር ሲዱ ጋር በኢስላም አባድ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የመከላከያ ሠራዊትን በዘመናዊ መልክ ለማዋቀር ስልታዊ ትኩረትን ጨምሮ ኢትዮጵያ በሁለንተናዊ የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል። የፓኪስታን አየር ኃይል ያለውን ጠንካራ የተግባር ዝግጁነት፣ እያደገ የመጣውን ሁለገብ ዘርፍ ችሎታዎች እና አስተማማኝ የመከላከል አቋም አድንቀዋል። ኤር ቺፍ ማርሻል ዛሂር አህመድ ባበር ሲዱ በበኩላቸው፤ ጉብኝቱ በሀገራቱ መካከል እያደገ የመጣውን ግንኙነት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። ፓኪስታን ከኢትዮጵያ ጋር ላላት ግንኙነት ከፍተኛ ዋጋ እንደምትሰጥ ጠቅሰው፤ የሀገራቸው አየር ኃይል በአቅም ግንባታ፣ በላቀ ስልጠና እና በክንውን ዘርፎች ለኢትዮጵያ አየር ኃይል ድጋፍ ለማድረግ ጽኑ አቋም እንዳለው አረጋግጠዋል። በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር) ጉብኝቱ በሁለቱ ወዳጅ ሀገራት አየር ኃይሎች መካከል ለአዲስ ስልታዊ የትብብር ምዕራፍ ጠንካራ መሰረት መጣሉን ገልፀዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች ይጠናከራሉ - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)
Aug 27, 2025 193
ሆሳዕና ፤ነሐሴ 21/2017 (ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡ "ሰላምን ማፅናት ለክልሉ ሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ዘላቂ ሰላምን በማጽናት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡ ለዚህም የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ትግበራን የማስፋትና የተጠናከረ የህግ ማስከበር ስራ ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል፡፡ ሰላምን ማስጠበቅና ማፅናት በክልሉ እየተመዘገበ ያለውን ፈጣን እድገት ለማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ የሀይማኖት ተቋማት፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የትምህርት ተቋማት በሰላም ግንባታ ላይ አበክረው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በዚህም በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ዘላቂ ሰላምን በማፅናት የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በበኩላቸው በክልሉ የፀጥታ መዋቅሩ ከህዝቡ ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ሰላምን በዘላቂነት ለማጽናት የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል፡፡ የክልሉ ፀጥታ ምክር ቤት አባል ወይዘሮ ጀሚላ ኢብራሂም፣ የሴቶችን አደረጃጀት በመጠቀም ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥና እድገትን ለማስቀጠል መስራት ይገባል ብለዋል። ሌላው የምክር ቤቱ አባል ወጣት ነስሩ ኡመር በበኩሉ በአካባቢው የህዝብ ለህዝብ ትስስር በማጠናከር ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየሰራን ነው ብሏል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን አስተዳዳሪዎች፣ የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አባላት፣ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግዎች ተሳትፈዋል፡፡
ማህበራዊ
በቀላሉ ማግኘት እየተቻለ ችላ የሚባለው ቫይታሚን ዲ
Aug 28, 2025 43
የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የቫይታሚን ዲ እጥረት ለተለያዩ በሽታዎች ሊያጋልጥ እንደሚችል ገልጸዋል። የቫይታሚን ዲ እጥረት የሚያስከትው ጉዳት፣ ለቫይታሚን ዲ እጥረት አጋላጭ ምክንያቶች፣ በቫይታሚን ዲ እጥረት ላለመያዝ መደረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች ባለሙያው ከታች በቀረበው መሠረት አብራርተዋል። • የቫይታሚን ዲ እጥረት የሚያስከትው ጉዳት O በልጆች እና ዐዋቂዎች የአጥንት ጤናማነት ላይ ጉዳት ያደርሳል። O የጡንቻዎች ድክመት ብሎም ህመም ሊከሰት ይችላል። O ድካም፣ የነርቭ ሥርዓት ህመም፣ የመንፈስ ጭንቀት ያጋጥማል። O የበሽታ መከላከያ ሥርዓትን በማዳከም ለበሽታዎች የመጋለጥ ዕድልን ይጨምራል። • አጋላጭ ምክንያቶች O በቂ ቀጥተኛ የሆነ የፀሐይ ብርሃን አለማግኘት፤ O ከምግብ በበቂ ሁኔታ ቫይታሚን ዲ አለማግኘት፤ O ጠቆር ያለ የቆዳ ቀለም (ተፈጥሯዊ አጋላጭ ምክንያት ነው)፤ O አለባባስ (ሙሉ ሰውነትን ከፀሐይ በሚከልል መልኩ መልበስ)፤ O በሽታዎች (እንደ ጉበት፣ ኩላሊት ያሉ ህመሞች ከምግብም ሆነ ከፀሐይ የምናገኘውን ቫይታሚን ዲ ሰውነታችን እንዲጠቀምበት ለመለወጥ በሚደረግ ሂደት ላይ ተጽዕኖ ያሳድራሉ)። O ውፍረት (በስብ ውስጥ የቫይታሚን ዲ መከማቸት)፤ O መድኃኒቶች (ለምሳሌ የአንቲሴዘር፣ የቲቢ፣ ስቴሮኢድስ፣ የአንጀት እንቅሰቃሴን የሚጨምሩ፣ የሃሞት ፈሳሽን ከሰውነት የሚያወጡ መድኃኒቶች)፤ • በበቫይታሚን ዲ እጥረት ላለመያዝ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ 👉 ደኅንነቱ የተጠበቀ የፀሐይ መጋለጥ (እንደ ቆዳ ዓይነት የሚወሰን ሆኖ በሣምንት ለጥቂት ጊዜያት በየቀኑ ከ10 እስከ 15 ደቂቃዎች)፤ 👉 በቫይታሚን ዲ የበለጸጉ ምግቦች (ሳልሞን፣ ሰርዲን፣ ወተት፣ ጥራጥሬ፣ የእንቁላል አስኳሎች፣ ጉበት) መመገብ፤ 👉 ከምግብ እና ከፀሐይ ብርሃን የሚገኘው የቫይታሚን ዲ በቂ ካልሆነ ተጨማሪ ቪታሚን ዲ መውሰድ፤ 👉 ከፍተኛ ተጋላጭነት ላለባቸው የሕብረተሰብ ክፍሎች (አረጋውያን፣ ጽኑ ህሙማን፣ ማላብሶርፕሽን ላለባቸው ሰዎች፣ በከተሞች አካባቢ ጥቁር ቆዳ ላለባቸው ሰዎች) ምርመራ ማድረግ፤ 👉 ከቤት ውጭ የሚደረግ እንቅስቃሴ (ከቤት ውጭ በተለይም ለልጆች እና ለአረጋውያን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጊዜን ማበረታታት)፤ 👉 ክብደትን መቆጣጠር (ከመጠን ያለፈ ውፍረት ከዝቅተኛ የቫይታሚን ዲ ጋር የተያያዘ ነው)፤ 👉 የአካል ብቃት እንቅስቃሴ (የአጥንት እና የጡንቻን ጤና ያሻሽላል፣ ከቫይታሚን ዲ ጋር በመተባበር ይሠራል)፤ • የቫይታሚን ዲ እጥረት ያለባቸው ሰዎች ምን አይነት ጥቃቄ እንዲያደርጉ ይመከራል? በአብዛኛው በከተማ የሚኖሩ ሰዎች ለቫይታሚን ዲ እጥረት ተጋላጭ መሆናቸውን ያነሱት ዶክተር ፍፁም፤ ለምሳሌ በመካከለኛ የትምህርት ዕድሜ ያሉ ልጆች በከተማ 61 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም በገጠር 21 ነጥብ 2 በመቶ የቫይታሚን ዲ እጥረት እንዳለባችው የጥናት ውጤት ማመላከቱን ጠቅሰዋል። የቫይታሚን ዲ እጥረትን ለማስተካከል በግል ከሚደረጉ ጥረቶች ባለፈ ወደ ሕክምና ተቋም በመሄድ በቃላሉ ማከም እንደሚቻልም ነው ያስገነዘቡት። በተለይም ለዚህ ችግር ተጋላጭ የሆኑ ማለትም የጉበት እና የኩላሊት እንዲሁም የማልአብዞርብሽን ችግር ያለባቸው ብሎም በክረምት ወቅት የተወለዱ ልጆች (በቂ የፀሐይ ብርሃን ስለማያገኙ ) የመድሃኒት ድጋፍ መውሰድ ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በሲዳማ ክልል ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ያተኮረ ኤች.አይ.ቪን የመከላከል እና የመቆጣጠር ሥራ እየተሰራ ነው
Aug 28, 2025 50
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ያተኮረ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ የመከላከል እና መቆጣጠር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የዘርፈ ብዙ ኤች. አይ. ቪ./ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር የ2017 በጀት አፈጻጻምና የቀጣይ ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሰላማዊት መንገሻ በዚህ ጊዜ እንደገለጹት በክልሉ ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎችንና አካባቢዎችን በመለየት የበሽታውን ስርጭት ለመከላከልና ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው፡፡ በዚህም ምርመራ፣ መድሃኒት የማስጀመርና የቫይረሱን ስርጭት መጠን ለመከታተል የሚያስችል የሕክምና አገልግሎት በጤና ተቋማት እየተሰጠ ነው ብለዋል፡፡ በሁሉም የጤና ተቋማት የቅድመ ወሊድ ክትትል ለሚያደርጉ እናቶች የኤች.አይ.ቪ ምርመራ አገልግሎት በመስጠት ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ዶክተር ሰላማዊት ገልጸዋል፡፡ በዚህም በ2030 አዲስ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ታማሚ እንዳይኖር የተያዘውን ሀገራዊ ግብ ለማሳካት የሚያስችል ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ በክልሉ ከመንግስት ሠራተኞች ደመወዝ ተቆርጦ ቫይረሱ በደማቸው ላለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሚውለውን ገንዘብ በአግባቡ ሰብስቦ ከመጠቀም አንጻር ያለውን ውስንነት መፍታት የቀጣይ ትኩረት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በቢሮው የኤችአይ.ቪ./ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ ታረቀኝ ታሪኩ በበኩላቸው እንዳሉት ሀዋሳ፣ ይርጋለም፣ አለታ ወንዶና ወንዶገነት ከተሞች የበሽታው ስርጭት ከፍተኛ ከሆነባቸው አካባቢዎች ይጠቀሳሉ። በከተሞቹ ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ፣ የምርመራና መድሃኒት እንዲጀምሩ የማድረግ ሥራ በመስራት ኤች አይ ቪን የመከላከልና መቆጣጠር ሥራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በስድስት ወራት በተከናወነ ተግባር ከ249 በላይ ነፍሰ ጡር እናቶች ቫይረሱ እንደተገኘባቸውና መድሃኒት እንደጀመሩ ተናግረዋል፡፡ በክልሉ ከሚገኙ የመንግስት ሠራተኞች የሚሰበሰበው የ0 ነጥብ 5 ከመቶ የኤድስ ፈንድ በተገቢው ከመሰብሰብና ከመጠቀም አንጻር በሚታዩ ክፍተቶች ላይ መድረኩ ትኩረት ሰጥቶ መምከሩንም ጠቅሰዋል፡፡ ሀዋሳ ከተማ ለኤች.አይ.ቪ ቫይረስ ተጋላጭ ከሆኑት ቀዳሚ መሆኗን የጠቀሱት የሃዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ ፣ በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የታገዘ የምርመራና የግንዛቤ ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎችን ለይቶ የሚከናወኑ የምርመራና ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እስከ ጤና ተቋማት የህክምና አገልግሎት እንደሚዘልቅ ጠቅሰው፣ ቫይረሱ ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ የሚያስችሉ ሥራዎችም እየተሰሩ ነው ብለዋል። በመድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢን ጨምሮ ከክልል ጀምሮ ባሉ መዋቅሮች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት የእውቅና ምስክር ወረቀትና ሽልማት የመስጠት መርሃ ግብርም ተከናውኗል።
በዩኒቨርሲቲው የተሰጠን ስልጠና የእውቀት አድማሳችንን አስፍቶልናል - ተማሪዎች
Aug 28, 2025 56
ወልዲያ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፡- በክረምቱ ወራት በዩኒቨርሲቲው የተሰጣቸው የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠና የእውቀት አድማሳቸውን ማስፋት እንዲችሉ እንዳገዛቸው ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ያሰለጠናቸው የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ተናገሩ። ወልዲያ ዩንቨርሲቲ በቢዝነስ ኢንኩቤሽን ማዕከሉ ባለፉት 2 ወራት በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህድስናና ሒሳብ ትምህርቶች ያሰለጠናቸውን ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን ዛሬ ሸኝቷል። ተማሪዎቹ በየትምህርት ደረጃቸው የላቀ ውጤት በማምጣት ተመልምለው በዩኒቨርሲቲው የሰለጠኑ እንደሆነ ተመልክቷል። ስልጠናውን በከፍተኛ ውጤት ያጠናቀቀችው ረድኤት መኮንን በሰጠችው አስተያየት፤ ቀደም ሲል በትምህርት ቤቷ በንድፈ ሀሳብ ያገኘችውን እውቀት በዩኒቨርሲቲው የክረምት ስልጠና ማዳበር እንደቻለች ተናግራለች። በዩኒቨርሲቲው የላቦራቶር፣ የማጣቀሻ መጻህፍት፣ የኮምፒውተር አገልግሎት የተሟሉለት በመሆኑ የዕውቀት አድማሴን አስፍቶልኛል ስትል ገልጻለች። ሌላው ሰልጣኝ ኤፍሬም መካሻ በበኩሉ፤ በዩኒቨርሲቲው የተሰጠው የንድፈ ሀሳብና የተግባር ትምህርት የቴክኖሎጂ ፈጠራ እንዲሰራና የእውቀት አድማሱን ማስፋት እንዲችል ያገዘው መሆኑን ተናግሯል። በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ማርዬ በለጠ (ዶ/ር) በሽኝት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፤ በስልጠናው ተማሪዎች በቂ ዕውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ ጥረት መደረጉን ገልጸዋል። ስልጠናውን የወሰዱት ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻቸው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም እንደ ክፍል ደረጃቸው በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና በሒሳብ ላይ ያተኮረ ትምህርት በብቁ መምህራን መስጠት መቻሉን አስረድተዋል። ዩኒቨርስቲው ከሰሜን ወሎ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ 150 ተማሪዎች ለስልጠናው የኮምፒውተርና ሌሎች የመማሪያ ቁሳቁሶች ከማሟላት በሻገር የምግብ፣ የመኝታ፣ የህክምናና የመጓጓዣ ሙሉ ወጪዎችን መሸፈኑን አንስተዋል። በቀጣይም ለሰልጣኝ ተማሪዎች በያሉበት አካባቢ ዩኒቨርሲቲው ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግ ማርዬ በለጠ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ በመፍጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በትጋት እየተሰራ ነው
Aug 28, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ሙስናን የሚፀየፍ ትውልድ በመፍጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በትጋት እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ገለጸ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና በ2018 ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡ በመዲናዋ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሙስናን በመከላከል አንድ ነጥብ አራት ቢሊዮን ብር የሚገመት ሃብት ከምዝበራ ማዳን መቻሉ በዚሁ ወቅት ተጠቁሟል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀማል ረዲ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በመዲናዋ ሙስናን ለመታገል ከሚወሰዱ እርምጃዎች በተጓዳኝ ሌብነትን የሚጸየፍ ትውልድ ለመገንባት እየተሰራ ነው። በከተማዋ የሙስናና ብልሹ አሠራር ተጋላጭነትን ለመቀነስ ሕብረተሰቡን ያሳተፈ የስነ-ምግባር ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድ በመንደፍ በሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስናን በመከላከል ውጤታማ ተግባራት አከናውኗል ብለዋል። በዚህም በአስቸኳይና በመደበኛ የሙስና መከላከል ሥራ አንድ ነጥብ አራት ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ሃብት ከምዝበራ ማዳኑን አስታውቀዋል። ኮሚሽኑ ብልሹ አሰራር የፈጸሙ ሠራተኞች፣ አመራር አባላት እና ባለጉዳዮች በህግ እንዲጠየቁ ማድረጉንም ጠቁመዋል። የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር መቅደስ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ በሥነ-ምግባር ግንባታና የኅብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል። በዚህም በትምህርት ቤቶች፣ በተለያዩ የእምነት ተቋማት እና በመንግሥትና በግል ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቁመዋል። ኮሚሽኑ የሀገርና የሕዝብን ሀብትና ንብረት ከምዝበራ ለማዳን በሚያከናውነው ተግባር ሕዝቡ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎችም በክፍለ ከተማ ደረጃ በሥነ-ምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ዘርፎች አመርቂ የሚባሉ ስራዎች መሠራታቸውን ተናግረዋል፡፡ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የሥነ-ምግባር እና ጸረ ሙስና መከታተያ ክፍል ቡድን መሪ ወይዘሮ ስንታየሁ ወዳጆ ሙስናን የሚጠየፍ ትውልድ ለመፍጠር በትምህርት ቤቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሥነ-ምግባር እና ጸረ ሙስና የስራ ሂደት መሪ ስለሺ አሰፋ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ ለሚገኙ ፈጻሚዎች በጸረ ሙስና ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የየካ ክፍለ ከተማ የሥነ-ምግባር እና ጸረ ሙስና ቡድን መሪ ወይዘሮ ናናቲ ገስሙ በበኩላቸው፤ ሙስናን ከመከላከል አኳያ የሁሉም ተሳትፎና እገዛ ሊኖር እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ኮሚሽኑ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በስነ-ምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት እውቅና ሰጥቷል፡፡
ኢኮኖሚ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል
Aug 28, 2025 54
ሆሳዕና፤ ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ወደሥራ መገባቱን የክልሉ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀምና የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በሆሳዕና ከተማ መክሯል፡፡ በዚህ ወቅት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሙስጠፋ ኢሳ እንደገለጹት በተጠናቀቀው የሥራ ዘመን የክልሉን ፀጋ መሰረት ያደረጉ አማራጮችን በመጠቀም የወጣቶችን የሥራ አጥነት ችግር ለማቃለል ሥራዎች ተከናውነዋል። ይህም ኢንተርፕራይዞችን በክህሎት ስልጠና ከመደገፍ ጀምሮ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን፣ በመስሪያና በመሸጫ ቦታ ዝግጅት፣ በብድር አቅርቦትና ተወዳዳሪ ማድረግ ላይ ያተኮረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ለ371 ሺህ 351 ወጣቶች የሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሥራ ዕድል በመፍጠር ከታቀደው በላይ ማከናወን መቻሉን አውስተዋል፡፡ በተያዘው የበጀት ዓመትም ከ400 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ለማድረግ ወደ ተግባር መገባቱን ነው ያመለከቱት። የሀድያ ዞን ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ሊረንሶ በበኩላቸው፤ በዞኑ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ምቹ መደላድል እየተፈጠረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በዚህም በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ የሥራ አማራጮችን በመለየት ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ወደ ተግባራዊ ሥራ ተገብቷል ብለዋል፡፡ በ2017 በጀት ዓመት ከ45 ሺህ ለሚበልጡ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩን የገለጹት ደግሞ የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታጁ ነስሩ ናቸው። በተያዘው በጀት ዓመትም ካለፈው የሥራ ዘመን ተሞክሮ በመውሰድ የወጣቱን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማስፋት ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ በእንጨትና የብረታ ብረት ማምረቻ ስራ ላይ የተሰማራው ወጣት ሄኖክ አንጁሎ፤ ዘንድሮ በተፈጠረለት የሥራ ዕድል ገቢ እያገኘ እራሱንና ቤተሰቡን በማስተዳደር ተጠቃሚ መሆኑን አመልክቷል። በምክክር መድረኩ በክልሉ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ሽግግር ኢኒቬቲቭ የዘርፉ ተዋንያንን የፕሮጀክት አፈፃፀም ለማሳደግ ያስችላል
Aug 28, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ሽግግር ኢኒቬቲቭ የዘርፉ ተዋንያንን የፕሮጀክት አፈፃፀም በማሳደግ በሌሎች አገራት ለመሳተፍ የሚያስችል አቅም ለመፍጠር እንደሚያግዝ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል ስምንተኛውን የመንገድ ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ አካሒዷል፡፡ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በኮንስትራክሽን ዘርፉ የተደረጉ ማሻሻያዎች ውጤት እያስመዘገቡ ነው፡፡ ብቃት ያለው ውጤታማና ተወዳዳሪ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለመፍጠር አገር አቀፍ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ሽግግር ኢኒቬቲቭ ገቢራዊ መደረጉን ገልጸዋል፡፡ በዚህም ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ፣ ወጭና ጥራት ማጠናቀቅ የሚያስችል የፕሮጀክት አፈፃፀም እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ የተቀመጡ ስትራቴጂዎች የዘርፉን ተወዳዳሪነት እያሳደጉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ኢኒሼቲቩ ኢትዮጵያውያን የሥራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎችና ባለሙያዎች በአፍሪካ አገሮች ጭምር በመሳተፍ ለኢትዮጵያ ገቢ ማመንጨት እንዲችሉ ያግዛቸዋል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብድራህማን በበኩላቸው፤ የመንገድ ዘርፍ በመንግስት ትኩረት ከተሰጣቸው የግንባታ ፕሮጀክቶች መካከለ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ለህብረተሰቡ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ በጀት የሚመደብላቸው ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በተያዘላቸው ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ማብቃት የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን የመልማት ፍላጎት የሚመልሱ መሆናቸውን በመግለጽ፤ ሪፎርሙ የመንገድ ምርምርን በማጠናከር የፕሮጀክት አፈፃፀም አቅምን ያሳድጋል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ወርቁ አስራቴ (ዶ/ር)፤ የመንገድ ምርምር ዘርፉን በዘላቂነት መደገፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ የፕሮጀክት አስተዳደር፣ የሀብት አጠቃቀም ውስንነቶች እንደነበሩ በማስታወስ፤ ዘርፉን በምርምር መደገፍ አስፈልጓል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በቴምር ልማት እምቅ አቅም ያላት ሀገር መሆኗን ማረጋገጥ ችለናል - የቴምር ፌስቲቫል ተሳታፊዎች
Aug 28, 2025 79
ሰመራ ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በቴምር ልማት እምቅ አቅም ያላት ሀገር መሆኗን በማየት ማረጋገጥ ችለናል ሲሉ በዓለም አቀፉ የቴምር ፌስቲቫል ላይ የተሳተፉ የተለያዩ አገራት ተወካዮች ተናገሩ። የመጀመሪያው ዓለም ዓቀፍ የቴምር ፌስቲቫል በርካታ የውጭና የሀገር ውስጥ ተሳታፊዎች በተገኙበት በአፋር ክልል ሠመራ ከተማ ለሶስት ቀናት ተካሂዶ በስኬት ተጠናቋል። በፌስቲቫሉ ላይ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡ የግብርና ሃላፊዎች፣ የዘርፉ ተመራማሪዎች፣ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮችና ተወካዮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በክልሉ የዘርፉን ልማት ጎብኝተዋል። በፌስቲቫሉ ላይ ከተገኙት መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው የተለያዩ አገራት ተሳታፊዎች ኢትዮጵያ ለቴምር ልማት ምቹ የአየር ንብረት፣ ሰፊ መሬትና ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ አሰራር ያላት መሆኑን ተገንዝበናል ብለዋል። ኢትዮጵያ በቴምር ልማት እምቅ አቅም ያላት ሀገር መሆኗን በአካል ተገኝተን በማየት ማረጋገጥ ችለናል ሲሉም ተናግረዋል። ከተሳታፊዎች መካከል ከሜክሲኮ የመጡት ሆርኬ አናያ፤ ከፌስቲቫሉ በተጓዳኝ በአፋር ክልል በነበረን ጉብኝት ኢትዮጵያ በተለይም በቴምር ልማት ምን ያክል እምቅ አቅም እንዳላት የተረዳንበት ነው ብለዋል። በአካባቢው በቴምር ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ ከተሰራ ከራስ አልፎ ለሌሎችም የሚጠቅም ምርት የሚገኝበት መሆኑን ጠቁመው፤ የተጀመረው እንቅስቃሴም ይህንኑ ለማሳካት የሚያስችል ጅምር መሆኑን አንስተዋል። ከሞሮኮ የመጡት አብዱላህ ሙስጠፋ፤ የፌስቲቫሉ መካሄድ ከተለያዩ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት ለመስራት እድል የፈጠረና የኢትዮጵያንም እምቅ አቅም ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል። ከፍተኛ የሥነ ምግብነት ጠቀሜታ ያለው ቴምር ሰፊ የገበያ አማራጭ እንዳለው ያነሱት አብዱላህ፤ በትብብርና ትኩረት ሰጥተን በማልማት ከኢትዮጵያም ባለፈ ለሌሎች አገራት የሚተርፍ ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። ከተርኪዬ በፌስቲቫሉ ላይ የተሳተፉት አማን ከድርበሺር፤ በዘርፉ የሚዘጋጁት መሰል ፌስቲቫሎችና ዐውደ ርዕዮች ቴምርን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዘን እንድናለማ ያግዘናል ብለዋል።
የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በዓለም አቀፍ የገበያ ሥርዐት ውስጥ ተወዳዳሪነቱን ጠብቆ ለመቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎችን እያከናወነ ነው
Aug 28, 2025 67
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በዓለም አቀፍ የገበያ ሥርዐት ውስጥ ተወዳዳሪነቱን ጠብቆ ለመቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን የኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊ ገለጹ። የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በላቦራቶሪ አስተዳደር ሥርአት "ISO-17025" ዛሬ የዕውቅና የምስክር ወረቀት አግኝቷል። በሀዋሳ ከተማ ዛሬ በተካሄደ የእውቅና አሰጣጥ ሥነሥርዐት ላይ የኢኮኖሚ ዞኑ ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ማቴዎስ አሸናፊ የምሥክር ወረቀቱን ከኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ተቀብለዋል። በዚህ ወቅት ሥራ እስኪያጁ የልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ዓለም አቀፍ የገበያ ሥርዐት ውስጥ ተወዳዳሪነቱን አስጠብቆ ለማስቀጠል የሚያስችሉ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የዞኑን ዓለም አቀፍ ዕውቅናና ተፈላጊነት የሚያሳድጉ የISO የእውቅና ምስክር ወረቀቶችን በተለያዩ ዘርፎች ለማግኘት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። ከዚህ ቀደም ዞኑ የፍሳሽ ውሃ አወጋገድ ሥርአቱ በአካባቢው አየር እና ማህበረሰብ ላይ ጉዳት የማያስከትል መሆኑን የሚያረጋግጥ የISO-14001 የዕውቅና ምስክር ወረቀት ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በውስጡ በሥራ ላይ የሚገኙ ኩባንያዎች ምርቶቻቸው በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ተቀባይነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸው፣ ለኢንቨስትመንት ወደ ዞኑ የሚመጡ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎችም ፍላጎታቸው ጨምሯል ብለዋል፡፡ ዛሬ በላቦራቶሪ አስተዳደር ሥርዐት የተገኘው የISO-17025 ደግሞ ለዞኑ ተጨማሪ ጥቅምና ዕውቅና እንደሚያስገኝ የተናገሩት አቶ ማቴዎስ፣ ከዚህ በፊት የሚጠቀሙበትን ውሃ ለማስፈተሽ ናሙና ወደ ውጭ ሀገር የሚልኩ ኩባንያዎች እዚሁ አስፈትሸው ለመጠቀም እንደሚያስችላቸው አስረድተዋል፡፡ ከዞኑ ውጭ ላሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ኢንዱስትሪዎች የፍተሻ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸው መሆኑንም ገልፀዋል። በሌላ በኩል የኢኮኖሚ ዞኑ እና በዞኑ ያሉ ኩባንያዎች ዓለም አቀፍ ገበያ ውስጥ ዕውቅናቸውና ተወዳዳሪነታቸው ይበልጥ እንዲጨምር ያግዛል ብለዋል። በቀጣይ በአጠቃላይ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት የሚያደርገውን የISO-9001 ዕውቅና ምስክር ወረቀት ለማግኘት ዞኑ የዝግጅት ሥራውን ማጠናቀቁንም አስታውቀዋል፡፡ በኃይል አጠቃቀም ሥርአት ላይ እንዲሁ ተጨማሪ ዕውቅና ለማግኘት በዞኑ በኩል የዝግጅት ሥራዎች መጀመራቸውን ነው አቶ ማቴዎስ ያስታወቁት፡፡ በኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት የላቦራቶሪ አክሪዲቴሽን መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌቴ ብርሀን ልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ በላቦራቶሪ አስተዳደር ሥርአቱ ባሉ ሶስት መለኪያዎች መሰረት የዕውቅና ምስክር ወረቀቱን እንዳገኘ አስረድተዋል፡፡ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ዓለም ዓቀፍ የላቦራቶሪ አክሪዲቴሽን ትብብር አባል መሆኑን አስታውሰው፣ ዞኑ ያገኘው የምስክር ወረቀት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሀዋሳ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ለሌሎች ተመሳሳይ ተቋማት አርአያ የሚሆን ሥራ እየሰራ መሆኑንም አቶ ጌቴ ገልጸዋል፡፡
ሳይንስና ቴክኖሎጂ
የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ሳይንስና ቴክኖሎጂን በተሻለ መንገድ ለመረዳት አስችሎናል - ታዳጊዎች
Aug 28, 2025 66
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ሳይንስና ቴክኖሎጂን በተሻለ መንገድ ለመረዳት የሚያስችል ግንዛቤን ያስጨበጣቸው መሆኑን ታዳጊዎች ገለፁ። አምስት የዐውደ ርዕይ ምድቦችን የያዘው የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ መከፈቱ ይታወሳል። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የኢትዮጵያ ምላሽ፣ ግብርና ቴክኖሎጂ፣ የውኃ ኃይል እና ኢነርጂ፣ ኤሮኖቲክስ እና አቪየሽን ላይ ያተኮሩ የዐውደ ርዕይ ምድቦች ይዟል። ኤግዚቢሽኑን ሲጎበኙ ኢዜአ ያነጋገራቸው ታዳጊዎች ጉብኝቱ የሰው ሰራሽ አስተውህሎትና ሌሎች ቴክኖሎጂዎችን በተሻለ መንገድ ለመገንዘብ እንደሚረዳ አብራርተዋል። ቋሚ ኢግዚቢሽኑን ሲጎበኝ ያገኘነው ህፃን ሞገስ ሚልኪያስ በኤግዚቢሽኑ ሮቦትና ሌሎች የሰው ሰራሽ አስተውሎትና የተለያዩ ዘርፎች ቴክኖሎጂዎችን መመልከቱን ተናግሯል። በእረፍት ጊዜው ኤግዚቢሽኑን መጎብኘቱ በትምህርት ቤት የተማራቸውን ነገሮች በተሻለ መንገድ እንዲረዳ እንዳስቻለው ገልጿል። ከአሜሪካ እንደመጣ የተናገረው ባርክኤል ዳዊት በበኩሉ በቋሚ ኤግዚቢሽኑ የተመለከታቸው ቴክኖሎጂዎች እንዳስደነቁት ነግሮናል። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያለን እውቀት ለማጎልበት የሚረዳ ነውም ብሏል። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ኢትዮጵያ በላቀ እድገት ላይ መሆኗን እንድገነዘብ አድርጎኛል ያለችው ደግሞ ሌላዋ ከአሜሪካ የመጣችው ኬብሮን ዳዊት ናት። ከሃዋሳ የመጣው ሶፎንያስ ተስፋዬ በበኩሉ ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ስለ ሰው ሰራሽ አስተውህሎትና የአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም ውሃና ኢነርጂ ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ እንደረዳው ይናገራል። ቋሚ ኤግዚቢሽኑ ትውልዱን ለፈጠራ የሚያነሳሳና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን ለመወሰን የሚረዳ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ዳዊት ዓለሙ ናቸው። አስተያየት ሰጪዎቹ ተማሪዎች በተለይ በቀሪ የእረፍት ጊዜያቸው ኤግዚቢሽኑን በመጎብኘት የተሻለ የሳይንስና ቴክኖሎጂ እውቀት እንዲጨብጡም መልዕክት አስተላልፈዋል። የአንድነት ፖርኮች ኮርፖሬሽን የህዝብ ግንኙነትና የኮሙዩኒኬሽን ባለሙያ ጌታቸው በየነ በበኩላቸው፤ የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን አሁን ላይ ያለውንና የወደፊቱን የቴክኖሎጂ ሁኔታ የሚያሳይ ነው ብለዋል። ሳይንስ ለአገር ግንባታ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው፤ ኤግዚቢሽኑ ትውልዱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ተገንዝቦ የፈጠራ ክህሎቱን እንዲያዳብር የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ውጤቶች ተገኝተዋል
Aug 28, 2025 71
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ ለሀገር እድገት የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ጥቅም ላይ በማዋል አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ተናገሩ። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የክልሎች የዘርፉ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም እና የተያዘው በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ላይ በድሬደዋ እየተወያዩ ነው። በውይይቱ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ የአገርን ከፍታና ዕድገት ለማረጋገጥ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በስፋትና በጥራት ስራ ላይ ማዋል ትኩረት ተሰጥቷል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና የፈጠራ ስራዎችን ወደ ተግባር በማሸጋገር በተቋማት በቴክኖሎጂ የታገዙ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎቶች በመስጠት አበረታች ውጤቶች መገኘታቸውን ገልጸዋል። የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች በመዘርጋትና ከክልሎች ጋር በመቀናጀት ረገድ በተከናወኑ ተግባራትም አብነታዊ ስራዎች መሰራታቸውን በማስታወስ። ከነዚህ በተጨማሪም የ'ስታርት አፕ' አዋጅ ፀድቆ ወደ ተግባር መሸጋገሩ የቴክኖሎጂ ፈጠራና ትውልዱ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት የድርሻውን እንዲወጣ መነቃቃት መፍጠሩን ተናግረዋል። በሰው ኃይል ልማትና ክህሎትም የአምስት ሚሊየን ኢትዮ- ኮዲንግ ስልጠናን ዜጎች በመውሰድ የዲጂታል ዕውቀታቸውን እንዲያሳድጉ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የሚፈለገውን ተወዳዳሪና ውጤታማ ዜጋ የማፍራቱን ሂደት ያጠናክረዋል ብለዋል። በድሬዳዋ የተጀመረው ውይይት እንደ አገርም ሆነ እንደ ድሬደዋ የተገኙ ውጤቶችን ለማጠናከር እና የተሻለ ለውጥ ለማምጣት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ያሉት ደግሞ በውይይቱ የተሳተፉት የድሬደዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ ናቸው። ምክትል ከንቲባው አክለው እንዳሉት በድሬዳዋ አስተዳደር ተቋማት የዲጂታል ቴክኖሎጂ እና አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶችን በመጠቀም ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎቶች ለህዝብ ተደራሽ እየተደረገ ነው። ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ውይይት ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች፣ እንዲሁም የክልሎች የዘርፉ አመራሮች ተሳታፊ ናቸው።
በሲዳማ ክልል የአንድ ማዕከል የመሶብ አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ
Aug 28, 2025 117
ሀዋሳ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ የአንድ ማዕከል የመሶብ አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለጹ። በክልሉ ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል። በሲዳማ ክልል የልማት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና አጠቃላይ የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችንና የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ በማብራሪያቸው ከለውጡ በኋላ በሲዳማ ክልል በሁሉም መስኮች የሚታዩና የሚጨበጡ ውጤቶች መመዝገባቸውንና ለህዝቡ የልማትና የአገልግሎት ፍላጎቶች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውንም አንስተዋል። በተለይም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት፣ ፈጣንና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ለመዘርጋት በልዩ ትኩረትና በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የልማት ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መዘርጋት የግድ መሆኑን አንስተዋል። በዚህም የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ የአንድ ማዕከል የመሶብ አገልግሎት ለማስጀመር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ለዚህም የሕንጻ፣ የሰው ሀይልና መሰል ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን አመልክተዋል። በከተማም ይሁን በገጠር ህዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ማሳካት እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ዝግጁነት ስለመኖሩም አስረድተዋል። የህዝብን ተጠቃሚነት የማረጋገጥና ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠት ጉዳይ በመንግስት ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድሩ ለመንግስት ሰራተኛው የደመወዝ ጭማሬ የማድረግ ውሳኔም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል። መንግስት የሚያደርገውን የደመወዝ ጭማሬ ተከትሎ የዋጋ ንረትና ያልተገባ እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ በሚሞክሩ አካላት ላይም ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ ገልጸው፤ ለዚህም ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደስራ ተገብቷል ብለዋል።
የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎትን ይበልጥ የሚያዘምን የቴክኖሎጂ ሥርዓት በቅርቡ ይተገበራል - ኤጀንሲው
Aug 27, 2025 198
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 21/2017(ኢዜአ)፦ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎትን ይበልጥ የሚያዘምን የቴክኖሎጂ ሥርዓት በቅርቡ እንደሚተገበር የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ። ከሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት መካከል የነዋሪነት አዲስ መታወቂያ ማውጣትና ማደስ፣ የልደት ፣ የሞት፣ የጋብቻ፣ የፍቺ እንዲሁም የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ማግኘት ይጠቀሳሉ፡፡ የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ ለኢዜአ እንደገለጹት ተቋሙ አገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል ባካሄደው ሪፎርም ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል። ሪፎርሙ በዋናነት በዘርፉ የነበረውን ብልሹ አሰራር መቅረፍ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፈጣን አሰራርን ተግባራዊ ማድረግ፣ አደረጃጀቶችን መቀየርና ምቹ የስራ ሁኔታ መፍጠር ላይ ትኩረት ማድረጉን ጠቅሰዋል። ኤጀንሲው በከተማዋ በ11 ቱም ክፍለ ከተሞች በሚገኙ 119 ወረዳዎች የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ በማድረግ ለነዋሪዎች ፈጣንና ቀልጣፋ መስተንግዶ ለመስጠት በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል። የተፈጠረው አሰራር ህገ ወጥ አካሄድን ከማስቀረቱ ባለፈ ቀደም ሲል በተቋሙ ይታይ የነበረውን የሃሰተኛ ሰነድ ዝግጅትና ስርጭት ለመከላከል፣ ለመቆጣጠርና ተጠያቂነትን ለማስፈን ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ነው ያሉት። በቴክኖሎጂ የታገዘው ፍትሃዊ፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራር ዜጎች ሳይጉላሉ የሚፈልጉትን አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻሉንም ተናግረዋል። በዘርፉ የሚሰጡ አገልግሎቶች በርካታ በመሆናቸው የማህበረሰቡን ፍላጎት በፍጥነት በመመለስ ረገድ ውስንነቶች መኖራቸውን ሃላፊው ጠቅሰዋል። በመሆኑም በዘርፉ የተገኙ ውጤቶችን ለማጠናከርና ጉድለቶቹን ለመሙላት አሰራሩን ይበልጥ ማዘመን አስፈላጊ መሆኑን ነው ያስታወቁት። ለዚህ የሚረዳ ዘመናዊና ዜጎች በቀላሉ የሚገለገሉበት ቴክኖሎጂ መልማቱን በመጠቆም ቴክኖሎጂው ተገልጋዮች የሚፈልጉትን አገልግሎት ባሉበት ቦታ ሆነው የሚያገኙበትን አሰራር የሚዘረጋና በዘርፉ የሚሰጠውን የዲጂታል አገልግሎት ከፍ የሚያደርግ ስለመሆኑ ጠቁመዋል። የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ያገኙ ተገልጋዮች በበኩላቸው በዲጂታል የታገዘ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል። በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት የልደት ካርድ ዲጂታል ለማድረግ የመጣችው ወጣት ዮርዳኖስ ኤርሚያስ አገልግሎት አሰጣጡ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዳገኝ ረድቶኛል ስትል ገልጻለች። በዚሁ ወረዳ የነዋሪነት ማረጋገጫ ሰነድ ለማውጣት የመጣው ወጣት ከተማ መርጊያ በበኩሉ ቀደም ሲል በወረዳው ይሰጥ የነበረው አገልግሎት የተንዛዛና የአሰራር ስርዓት ያልተበጀለት እንደነበር አስታውሷል። ወረዳው አሁን ላይ አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ በማዋሉ ቀልጣፋና ፍትሃዊ መስተግዶ ለማግኘት አንዳስቻላቸው ነዋሪዎቹ አስታወቀዋል፡፡ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ መታወቂያ ለማሳደስ የመጡት ወይዘሮ አልማዝ ወልደሰንበት እና አቶ ኑሩ አብዱራህማን የጽህፈት ቤቱ ሙያተኞቸ ያደረጉላቸው ትብብር የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ነዋሪዎቹ በወረዳው እየተሰጠ ያለው አገልግሎት ቀጣይነት እንዲኖረው አንስተው፤ የአሰራሩ መሻሻል ቀደም ሲል የነበረውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የመለሰ በመሆኑ ተግባሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
ስፖርት
የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ድልድል ይፋ ሆነ
Aug 28, 2025 63
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦የ2025/26 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ድልድል ዛሬ ማምሻውን በሞናኮ ይፋ ሆኗል። ውድድሩ መስከረም 6 ቀን 2018 ዓ.ም ይጀመራል። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ከባለፈው የውድድር ዓመት አንስቶ ሻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ድልድል ፎርማትን በማስቀረት 36 ክለቦች በ4 ቋቶች (Pots) በመከፋፈል እንዲጫወቱ የሚያደርግ አዲስ አሰራር መተግበር መጀመሩ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት 36ቱ ቡድኖች በ4 ቋቶች የተደለደሉ ሲሆን በእያንዳንዱ ቋት 9 ክለቦች ይገኛሉ። በቋት አንድ የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ፒኤስጂ፣ ሪያል ማድሪድ፣ ማንችስተር ሲቲ፣ ባየር ሙኒክ፣ ሊቨርፑል፣ ኢንተር ሚላን፣ ቼልሲ፣ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ እና ባርሴሎና ተደልድለዋል። አርሰናል፣ ባየር ሌቨርኩሰን፣ አትሌቲኮ ማድሪድ፣ ቤኔፊካ፣ አትላንታ፣ ቪያሪያል፣ ጁቬንቱስ፣ ኢንትራክት ፍራንክፈርት እና ክለብ ብሩዥ በቋት ሁለት የሚገኙ ናቸው። በቋት ሶስት ቶተንሃም ሆትስፐርስ፣ ፒኤስቪ አይንድሆቨን፣ አያክስ፣ ናፖሊ፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን፣ ኦሎምፒያኮስ፣ ስላቪያ ፕራግ፣ ቦዶ ግሊምት እና ማርሴይ ተገናኝተዋል። ኮፐንሃገን፣ ሞናኮ፣ ጋለታሳራይ፣ ሴንት ዩኒየን ጊሎስ፣ ካራባግ፣ አትሌቲኮ ቢልባኦ፣ ኒውካስትል ዩናይትድ፣ ፓፎስ እና ካይራት አልማቲ በቋት አራት የተደለደሉ ክለቦች ናቸው። አንድ ክለብ በራሱ ቋት ካለ ሁለት ቡድንና በእያንዳንዱ ቋት ካሉ ሁለት ክለቦች ጋር ጨዋታውን ያደርጋል። በዚህም አንድ ክለብ ስምንት ጨዋታ ያደርጋል። ከ36 ክለቦች መካከል በስምንት ጨዋታዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ስምንት ቡድኖች በቀጥታ ወደ ጥሎ ማለፉ ይገባሉ። ቀሪዎቹ ስምንት ወደ ጥሎ ማለፉ የሚገቡ ቡድኖች በሁለት የማጣሪያ ዙሮች ተጫውተው 16ት ውስጥ ይገባሉ። ከጥሎ ማለፉ አንስቶ ያለው የውድድር ፎርማት ከዚህ ቀደም ከነበረው ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው። ከዚህ ቀደም በውድድሩ ላይ ይሳተፉ የነበሩ 32 ክለቦች በአሁኑ የውድድር አሰራር ወደ 36 ከፍ ማለታቸው ይታወቃል።
ሞሮኮ ለፍጻሜ አለፈች
Aug 27, 2025 179
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2017(ኢዜአ)፦ በስምንተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና (ቻን) የግማሽ ፍጻሜ መርሃ ግብር ሞሮኮ ሴኔጋልን በመለያ ምት በማሸነፍ ለፍጻሜ ደርሳለች። ማምሻውን በማንዴላ ብሄራዊ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጆሴፍ ላዩስ ሳምብ በ16ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠረው ግብ ሴኔጋል መሪ ሆናለች። ብዙም ሳይቆይ ሳቢር ቡጅሪን በ23ኛው ደቂቃ ከመረብ ላይ ያሳረፈው ጎል ሞሮኮን አቻ አድርጓል። መደበኛው 90 ደቂቃ ግብ በአቻ ውጤት በመጠናቀቁ 30 ደቂቃ ተጨምሯል። በጭማሪው ሰዓት ግብ ባለመቆጠሩ ጨዋታው ወደ መለያ አምርቷል። በዚህም የሁለት ጊዜ የቻን አሸናፊዋ ሞሮኮ 5 ለ 3 በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፋለች። ከማዳጋስካር ጋር ዋንጫውን ለማንሳት ትፋለማለች። የወቅቱ የውድድሩ አሸናፊ ሴኔጋል ክብሯን ማስጠበቅ አልቻለችም። ዛሬ ቀን ላይ በተደረገው የመጀመሪያ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ማዳጋስካር ሱዳንን 1 ለ 0 ማሸነፏ ይታወቃል። የፍጻሜው ጨዋታ ቅዳሜ ነሐሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ይካሄዳል። የግማሽ ፍጻሜ ተሸናፊዎቹ ሴኔጋል እና ሱዳን አርብ ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ሶስተኛ ደረጃን ለማግኘት ይጫወታሉ። በታንዛንያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ ጣምራ አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው ቻን በሀገር ውስጥ ሊግ የሚገኙ ተጫዋቾች ብቻ የሚሳተፉበት ውድድር ነው።
ማዳጋስካር ለፍጻሜ አለፈች
Aug 26, 2025 178
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2017(ኢዜአ)፦ በስምንተኛው የአፍሪካ አገራት ሻምፒዮና (ቻን) የግማሽ ፍጻሜ መርሃ ግብር ማዳጋካስካር ሱዳንን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜ ደርሳለች። ማምሻውን በቤንጃሚን ምካፓ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ በመደበኛው 90 ደቂቃ ግብ ባለመቆጠሩ 30 ደቂቃ ተጨምሯል። በጭማሪው ሰዓት የ24 ዓመቱ አጥቂ ቶኪ ኒያና ራኮቶንድራይቤ በ116ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ማዳጋስካርን ባለድል አድርጋለች። የማዳጋስካሩ ፌኖሃሲና ጊሌስ ራዛፊማሮ በ79ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። በጨዋታው ማገባደጃና ጭማሪ ሰዓት ላይ የአንድ ተጫዋች ብልጫ ወስዳ የተጫወተችው ሱዳን እድሏን መጠቀም አልቻለችም። በአንጻሩ ማዳጋስካር ጠንካራ የአልሸነፍ ባይነት መንፈስ አሳይታለች። ውጤቱን ተከትሎ ማዳጋስካር ለፍጻሜው ያለፈች የመጀመሪያ ሀገር ሆናለች። በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የፍጻሜ ተፋላሚ ሆናለች። ሱዳን በቻን ተሳትፎዋ ለመጀመሪያ ጊዜ ለፍጻሜ የማለፍ ህልሟ አልተሳካም። ማዳጋስካር በፍጻሜው ከሴኔጋልና ሞሮኮ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች። ሴኔጋል እና ሞሮኮ በአሁኑ ሰዓት ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በካፍ የሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን የማጣሪያ ተጋጣሚዎቹን አውቋል
Aug 26, 2025 176
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በ2025/26 የካፍ የሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሀገራት የእግር ኳስ ማህበራት ምክር ቤት (ሴካፋ) ዞን ማጣሪያ በምድብ ሁለት ተደልድሏል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የቻምፒዮንስ ሊግ የማጣሪያ ዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ዛሬ በተቋሙ ዋና መቀመጫ ግብጽ ዋና ከተማ ካይሮ ላይ አከናውኗል። ኢትዮጵያን በሴካፋ ዞን ወክሎ በማጣሪያ ውድድሩ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በምድብ ሁለት ከብሩንዲው ቶፕ ገርልስ አካዳሚ እና ከሩዋንዳው ራዮን ስፖርትስ ተደልድሏል። የኬንያው ኬንያ ፖሊስ ቡሌትስ፣ የኤርትራው ደንደን እና የዩጋንዳው ካምፓላ ኩዊንስ በምድብ አንድ የተደለደሉ ክለቦች ናቸው። በምድብ ሶስት የታንዛንያው ጄኬቲ ኩዊንስ፣ የደቡብ ሱዳኑ ዬ ጆይንት ስታርስ እና የዛንዚባሩ ጄኬዩ ፕሪንሰስ ክለቦች በምድብ ሶስት ተደልድለዋል። የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ከነሐሴ 29 2017 ዓ.ም እስከ መስከረም 6 ቀን 2018 ዓ.ም በኬንያ አዘጋጅነት ይካሄዳል። ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በማጣሪያ ውድድሩ የሚሳተፈው የዘንድሮው የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ ነው። ንግድ ባንክ በካፍ የሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ ሲሳተፍ የዘንድሮው ለአምስተኛ ተከታታይ ዓመት ነው። ክለቡ ከዚህ ቀደም ባደረጋቸው አራት ተሳትፎዎች በ2016 ዓ.ም የሴካፋ ዞን ማጣሪያን በማሸነፍ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ መሳተፉ የሚታወስ ነው። ካፍ በዘንድሮው የማጣሪያ ውድድር 38 ክለቦች በስድስት ዞኖች ተከፍለው ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ አስታውቋል።ክለቦቹ የካፍ የክለብ ላይሰንሲንግ መስፈርቶችን ማሟላታቸውንም ገልጿል። በስድስቱ ዞኖች የሚያሸንፉ 6 ሀገራት፣ የወቅቱ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊ የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎው ቲፒ ማዜምቤ አና የውድድሩን የመጨረሻ ዙር የምታዘጋጀው ግብጽ አንድ ቡድን ጨምሮ 8 ክለቦች እ.አ.አ በ2026 ዋንጫውን ለማንሳት ይፋለማሉ። የካፍ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የተጀመረው እ.አ.አ በ2020 ነው። የደቡብ አፍሪካው ማሜሎዲ ሳንዳውንስ ሁለት ጊዜ ዋንጫውን ያነሳ ሲሆን የሞሮኮው ኤኤስ ፋር ራባት እና የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎው ቲፒ ማዜምቤ ውድድሩን አንድ አንድ ጊዜ አሸንፈዋል።
አካባቢ ጥበቃ
ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆን ይገባዋል
Aug 28, 2025 56
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ጽዱ ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆን እንደሚገባው የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ ገለጹ፡፡ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወሳል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አዋጁ ተግባራዊ በሚሆንበት አግባብ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ሰጥቷል። የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ እንዳሉትም፤ አዋጁ ከያዛቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል የፕላስቲክ ቆሻሻ አያያዝና የአወጋገድ ስርዓት ይገኝበታል፡፡ የፕላስቲክ ውጤቶች በመሬት ውስጥ ሳይበሰብሱ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ በመሆናቸው ለአካባቢ ብክለት መንስዔ፣ ለሰው ልጅ ጤና ደግሞ ጉዳት እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የሚጣጣም እና ዘመኑን የሚዋጅ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ማዘጋጀቷን ጠቁመዋል። በአዋጁ መሠረት ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት፣ ማምረትና ለገበያ ማቅረብ እንደማይቻል አመልክተዋል። ይህም ከስድስት ወራት በኋላ በመላው ሀገሪቷ ተፈጻሚ እንደሚሆን ተናግረዋል። በአካባቢም ሆነ በሰዎች ጤና ላይ ጉዳት የማያደርሱ ምርቶችን ለማቅረብ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። የዛሬው ስልጠናም አዋጁ በአግባቡ እንዲፈጸም ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ እንዲይዙ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የከተማ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ክትትል ዴስክ ሃላፊ ዋሲሁን አለሙ፤ ጽዱና ለኑሮ ምቹ አካባቢ ለመፍጠር እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ የፕላስቲክ ቆሻሻ አያያዝና የአወጋገድ ስርዓት ዙሪያ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቂ ግንዛቤ በመያዝ የበኩላቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ተስፋዬ ደጀኔ፤ ስልጠናው አዋጁን ተፈጻሚ ለማድረግ የጋራ አቋምና አቅም እንድንይዝ የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ዘመኑን የሚዋጅ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስርዓትን ተግባራዊ ታደርጋለች
Aug 28, 2025 54
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የሚጣጣም እና ዘመኑን የሚዋጅ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድን ተግባራዊ እንደምታደርግ የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ለሊሴ ነሜ ገለጹ። ዋና ዳይሬክተሯ እንደገለጹት ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን የሚከለክለው አዋጅ ከስድስት ወር በኋላ ይተገበራል ብለዋል። የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወሳል። ባለስልጣኑ አዋጁ ተግባራዊ በሚሆንበት አግባብ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት እየተሰጠ ባለው የስልጠና መድረክ ላይ ዋና ዳይሬክተሯ እንደገለጹት አዋጁ ከያዛቸው አንኳር ጉዳዮች መካከል የፕላስቲክ ቆሻሻ አያያዝና የአወጋገድ ስርዓት ይገኝበታል። የፕላስቲክ ውጤቶች በመሬት ውስጥ ሳይበሰበሱ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ በመሆናቸው ለአካባቢ ብክለት መንስዔ፣ ለሰው ልጅ ጤና ደግሞ ጉዳት እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል። በመሆኑም ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የሚጣጣም እና ዘመኑን የሚዋጅ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ማዘጋጀቷን ገልጸዋል። በአዋጁ መሠረትም ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት፣ ማምረትና ለገበያ ማቅረብ እንደማይቻል አመልክተዋል። ይህም ከስድስት ወራት በኋላ በመላው ሀገሪቱ ተፈጻሚ እንደሚሆን ተናግረዋል። በአካባቢም ሆነ በሰዎች ጤና ላይ ጉዳት የማያደርሱ ምርቶችን ለማቅረብ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና ከአምራች ዘርፉ ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። የዛሬው ስልጠናም አዋጁ በአግባቡ እንዲፈጸም ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ እንዲይዙ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል። ለቀጣዩ ትውልድ ጽዱ ኢትዮጵያ ለማስተላለፍ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑንም አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ አየር ንብረትና በአፍሪካ-ካሪቢያን ጉባኤዎች አህጉራዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ መሪ ሚናዋን ትወጣለች
Aug 28, 2025 109
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 22/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አየር ንብረትና በአፍሪካ-ካሪቢያን ጉባኤዎች ብሔራዊና አህጉራዊ ጥቅሞችን የሚያስጠበቁ አጀንዳዎችን በማቅረብ መሪ ሚናዋን እንደምትወጣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ገለጹ። አምባሳደር ነብያት በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች በሰጡት መግለጫ፤ኢትዮጵያ የአፍሪካ ካሪቢያን ማህበረሰብ እና ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤዎች በስኬት ለማስተናገድ ዝግጅት ማድረጓን ገልጸዋል። ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አፍሪካ በብራዚል በሚካሄደው 30ኛው የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ላይ የራሷን ድምፅ ይዛ የምትቀርብበትን ዕድል እንደሚፈጥርም ጠቁመዋል። በአዲስ አበባ በሚከናወነው ጉባኤ ከ25 ሺህ በላይ ታዳሚዎች እንደሚሳተፉ ገልጸው፣ አፍሪካውያን የአየር ንብረት ለውጥን ተፅዕኖን ለመቋቋም የጋራ የሆነ አፍሪካዊ ስልት የሚቀይሱበት መድረክ እንደሚሆንም ተናግረዋል። ከዚህም ባሻገር የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን ለመቋቋም ዓለም አቀፍ ፋይናንስ ለማፈላለግ እንደሚያግዝ ገልጸዋል። ኢትዮጵያ በጉባኤው ሀገራዊና አህጉራዊ አጀንዳን በማቅረብ መሪ ተዋናይ እንደምትሆን ጠቅሰው፥ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን የመከላከል ውጤታማ ተሞክሮዋን እንደምታካፍልም አንስተዋል። በተጨማሪም የአፍሪካ ካሪቢያን ማህበረሰብ ጉባኤ "ለአፍሪካውያንና ዘርዓ አፍሪካውያን የማካካሻ ፍትህን ለመሻት አህጉር ተሻጋሪ አጋርነት" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄድ ሲሆን የጋራ ድምፅ ማሰማት እንዲችሉ መሰረት እንደሚሆን ገልጸዋል። ጉባኤው የአፍሪካና ካሪቢያን ሀገራት በደቡብ ደቡብ የትብብር መንፈስ ግንኙነታቸውን ለማጎልበት፣ አፍሪካ ከካረቢያን ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ወደ ጠንካራ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ እና ትብብር ለማሳደግ ያስችላታል ብለዋል። ጉባኤው በዓለም የፋይናንስ ስርዓት፣ በቱሪዝም፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ እንደሚመክር ገልጸው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የካሪቢያን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት ዕድሎች እንዲሰማሩ ይደረጋል ነው ያሉት። አምባሳደር ነብያት በመግለጫቸው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያበስር ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለቅኝ ግዛት እሳቤዎች ቦታ የላትም ያሉት አምባሳደር ነብያት፣ በጋራ ተጠቃሚነትና ልማት ላይ የተመሰረተ ፅኑ ፍላጎት እንዳላት ገልጸዋል። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የተላከ መልዕክትን ለደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ማድረሱን ጠቅሰዋል። በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ትብብር መሰረት በኃይል፣ አቪየሽን፣ በመንገድ ስራና ሌሎች ዘርፎች በጋራ መስራት የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት መደረጉን ተናግረዋል። ይህም ኢትዮጵያ በቀጣናው ልማትና ትብብር ያላትን የተግባር እርምጃና ጽኑ አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ጉባኤው ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ልምዷን ለሀገራት የምታጋራበት ነው
Aug 27, 2025 171
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 21/2017(ኢዜአ)፦ ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እያከናወነች ያለውን የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ልምዷን ለሀገራት የምታጋራበት መሆኑ ተገለፀ። ኢትዮጵያ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ታስተናግዳለች። በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጥበቃና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈፃሚና የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ብሄራዊ ቴክኒክ ኮሚቴ ጸሐፊ ፋኖሴ መኮንን እንዳሉት ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በርካታ ስራዎችን እያከናወነች ትገኛለች። ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ አንፃር ህብረተሰቡን በማስተባበር በተከናወኑ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ከ33 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት እንዲያገግም ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት። በክረምቱ መርሃ ግብር በስነ-ህይወታዊ አፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ይህንን የማጠናከር ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዚህ ረገድ በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ያስቻለ መሆኑን ጠቁመው፤ የደረቁ የውሃ አካላት መልሰው እንዲያገግሙ ማድረጉን ተናግረዋል። በፕላንና ልማት ሚኒስቴር የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነትና ስትራቴጂክ አጋርነት መሪ ስራ አስፈፃሚ መንሱር ደሴ፥ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያስችሉ ፖሊሲና ስትራቴጂዎች እየተተገበሩ መሆኑን ተናግረዋል። ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የአረንጓዴ አሻራ፣ ታዳሽ ኃይል፣ ትራንስፖርትና ሌሎችም ስራዎች ተጨባጭ ውጤት የመጣባቸው የአረንጓዴ ልማት ዘርፎች ናቸው ብለዋል። ኃላፊዎቹ አክለውም ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ እያከናወነች ያለችው ተግባር ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን በጋራ የመልማት ትብብርን እያጠናከረ እንደሚገኝ አንስተዋል። ለሌሎች የአፍሪካ እና የዓለም ሀገራትም ትልቅ ተሞክሮ መሆኑን ጠቅሰው፥ ጉባኤው አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ምላሽ እያከናወነች ያለችውን ተግባር ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የምታሳይበት መሆኑን ተናግረዋል።
ዓለም አቀፍ ዜናዎች
የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በአህጉራዊ ትስስር ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ
Aug 26, 2025 216
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20/2017(ኢዜአ)፦የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) በአህጉራዊ ትስስር አጀንዳ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ለማላቅ እንደሚሰሩ አስታወቁ። በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ዋና ፀሐፊ ክላቫር ጋቴቴ ጋር ተወያይተዋል። ሁለቱ ወገኖች አፍሪካ በዓለም መድረክ አንድ የጋራ ድምጽ እንዲኖራት ማድረግ ያለውን ወሳኝ ጠቃሜታ አጽንኦት ሰጥተው መክረውበታል። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ በንግድ፣ቀጣናዊ ትስስር እና የአፍሪካ የአዕምራዊ ንብረትን የበለጠ አጀንዳ ማራመድ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በዓለም የንግድ ድርጅት(ጄኔቫ) የአፍሪካ ህብረት ቋሚ መልዕክተኛ ሆነው በሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም መሾማቸው የሚታወስ ነው። የአፍሪካ ህብረት እና ኢሲኤ ትብብራቸውን እ.አ.አ በ1960ዎቹ መግቢያ ላይ መጀመራቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ።
አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር ይሰራሉ
Aug 24, 2025 271
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 18 /2017 (ኢዜአ)፦አፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የበለጠ ለማጎልበት በትብብር እንደሚሰሩ አስታወቁ። ዘጠነኛው የጃፓን አፍሪካ ልማት ዓለም አቀፍ ፎረም(ቲካድ) በዮካሃማ መካሄዱን ቀጥሏል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከፎረሙ ጎን ለጎን ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ፕሬዝዳንት አኪሂኮ ታናካ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል። የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የጃይካ ከአፍሪካ ህብረት ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እንዲሁም ኢኮኖሚና ማህበራዊን ጨምሮ በአፍሪካ ቁልፍ ዘርፎች እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት አድንቀዋል። ሊቀ መንበሩ እና ፕሬዝዳንቱ የአፍሪካ ህብረት እና ጃፓን ያላቸውን የጋራ ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። ዘጠነኛውን የቲካድ ፎረም መንፈስ ወደ ዘላቂ የኢኮኖሚ ለውጥ በጋራ የመፍጠር ምዕራፍ ማሸጋገር እንደሚገባም አንስተዋል። ከነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው ፎረም የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ኢዜአ ከአፍሪካ ህብረት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ፤ የአህጉር በቀል መፍትሄዎች መድረክ
Aug 23, 2025 269
በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን የአየር ንብረት በርቀት የሚያዩት ስጋት ሳይሆን የዕለት ተዕለት እውነታቸው ነው። በጎርፍ ምክንያት የሚሞቱ ሰዎች እና ተጠራርገው የሚወሰዱ ንብረቶች፣ በተከታታይ ድርቆች ምክንያት የሚያጋጥመው የምርታማነት መቀነስ የአየር ንብረት ለውጥ ከወለዳቸው ቀውሶች መካከል ይጠቀሳሉ። እነዚህ በተጨባጭ የዜጎችን ኑሮ እየተፈታተኑ ያሉ ችግሮች በአፍሪካ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስነ ምህዳር ላይ ለውጥ እንዲመጣ አስገድደዋል። የድህነት ምጣኔ እና የተፈናቃይ ዜጎች እየጨመረ መምጣት የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎችን በተግባር የገለጡ ጉዳዮች ሆነዋል። አፍሪካ ለዓለም የበካይ ጋዝ ልቀት ከአራት በመቶ በታች ድርሻ ቢኖራትም የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳት ከፍተኛ ቀንበር የሚያርፍባት አህጉር ሆናለች። ከሳህል ቀጣና የበረሃማነት መስፋፋት እስከ ምስራቅ አፍሪካ ኃይለኛ ጎርፎች የአህጉሪቷ ዜጎች በጣም ውስን ድርሻ ባላቸው ጉዳይ የቀውሱ ከፍተኛ ሰላባ እየሆኑ ነው። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ የአስቸኳይ ጊዜ ውስጥ ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም። እንደ ዓለም አቀፉ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት መረጃ ከእ.አ.አ 1991 እስከ 2022 ባለው ሶስት አስርት ዓመታት ባሉ እያንዳዱ አስርት ዓመታት በአፍሪካ በአማካይ የ0 ነጥብ 3 ዲግሪ ሴልሺየስ የሙቀት ጭማሪ ተመዝግቧል። እ.አ.አ በ2024 የዓለም ሙቀት በ1 ነጥብ 2 ዲግሪ ሴልሺየስ ጨምሮ በዓለም ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተመዘገበበት ዓመት ነበር። 2024 በአፍሪካ የሙቀት መጠን 0 ነጥብ 86 በመቶ በመጨመር በአህጉሪቷ ታሪክ ከፍተኛው ሙቀት የተዘመገበበት ዓመት ሆኖም ተመዝግቧል። ከሙቀቱ በአሳሳቢ ሁኔታ መጨመር ባሻገር ድርቅ፣ ጎርፍ እና የምግብ ዋስትና ስጋት ላይ መውደቅ ሌሎች የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች ናቸው። እ.አ.አ 2024 ደቡባዊ አፍሪካ ክፍል በቅርብ አስርት ዓመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ድርቅ አጋጥሟታል። በድርቁ ምክንያት ዛምቢያ እና ዚምባቡዌ የሰብል ምርታቸው በ50 በመቶ ቀንሷል። በምስራቅ እና ማዕከላዊ አፍሪካ በቅርብ ጊዜ የተከሰቱ ከባድ ጎርፎች ሚሊዮኖችን አፈናቅለዋል፤ የዜጎች ህይወት አመሰቃቅላዋል መሰረተ ልማቶችንም አውድመዋል። የዓለም አቀፉ ሜትሮሎጂ ድርጅት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ደግሞ የአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካን ከሁለት እስከ አምስት በመቶ ጥቅል ዓመታዊ ምርት (ጂዲፒ) ወጪ እየወሰደ ይገኛል። አንዳንድ ሀገራት ለአየር ንብረት አስቸኳይ ምላሽ ዘጠኝ በመቶ ጥቅል ሀገራዊ ምርታቸውን ፈሰስ ያደርጋሉ። አፍሪካ በየዓመቱ ከ30 እስከ 50 ቢሊዮን ዶላር ለአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ አቅዶች ትግበራ ቢያስፈልጋትም ከዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ ውስጥ የምታገኘው ገንዘብ ከአንድ በመቶ በታች ነው። የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት የ2024 የአፍሪካ ሪፖርት የአፍሪካ የግብርና ምርታማነት ከእ.አ.አ 1961 በኋላ በ34 በመቶ መቀነሱን ይገልጻል። የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ ሀገራት ምግብ ለመግዛት የሚያወጡት 35 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ወጪ እ.አ.አ በ2025 ማብቂያ ወደ 110 ቢሊዮን ዶላር ገደማ ከፍ እንደሚል ገልጿል። የበረሃማነት መስፋፋት፣ የብዝሃ ህይወት መመናመን፣ የጤና እክሎች፣ መፈናቀል እና የታሪካዊ ቅርሶች አደጋ ላይ መውደቅ አፍሪካ እየገጠሟት ያሉ የአየር ንብረት ለውጥ አሉታዊ ተጽእኖዎች ውጤት ናቸው። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት በየዓመቱ 250 ቢሊዮን ዶላር ቢያስፈልጋትም እያገኘች ያለችው 30 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። የአየር ንብረት ለውጥ ስጋት አፍሪካ የጥያቄ አምሮት ኖሮባት የምታነሳው አጀንዳ ሳይሆን የፍትህ እና የህልውናዋ ጉዳይም ጭምር ነው። በአዲስ አበባ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፥ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" በሚል መሪ ሀሳብ የሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ አህጉሪቷ እየገጠሟት ካሉ አንገብጋቢ ፈተናዎችን በዘላቂነት መሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ይመክራል። የሀገራት መሪዎች፣ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች፣ የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋማት፣ ወጣቶች እና የግሉ ዘርፍ በአንድነት ይወያያሉ። በጉባኤው ላይ አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ በታዳሽ ኢነርጂ፣ ዘላቂ ግብርና እና ተፈጥሮ ተኮር መፍትሄዎች ጨምሮ በአፍሪካ ያሉ አረንጓዴ የመፍትሄ ሀሳቦች የበለ ማላቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሀገራት ተሞክሯቸውን ያቀርባሉ። አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራ በየዓመቱ የሚያጋጥማትን የ220 ቢሊዮን ዶላር የፋይናንስ አቅርቦት ክፍተት መሙላት እና አማራጭ የፋይናንስ ምንጮችን መጠቀም ላይ ምክክር ይደረጋል። በብራዚል ቤለም በሚካሄደው 30ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ 30) ጨምሮ በዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ድርድሮች ላይ የአፍሪካን ፍላጎቶች እና ጥቅሞች ማስጠበቅ የሚያስችል የጋራ እና ጠንካራ አቋም መያዝ ከጉባኤው የሚጠበቅ ውጤት ነው። የአፍሪካ ሀገራት በጉባኤው ላይ የአየር ንብረት ለውጥ ለመከላከል የሚያስችሉ ተጨባጭና መሬት ላይ የወረዱ እቅዶቻቸው ላይ የሚያቀርቡ ሲሆን የገቡትን ቃል ኪዳን ወደ ተግባር መቀየራቸውን የሚከታተል የቁጥጥር ስርዓት ትግባራትን የሚያጠናክሩባቸው መንገዶችን በማቅረብ በአጠቃላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ቃልኪዳናቸውን ዳግም ያድሳሉ። አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ችግሮች ገፈት ቀማሽ ሳትሆን የመፍትሄዎች እና የአይበገሬነት ስራዎች ማሳያም ናት። የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ እና አከባቢ ጥበቃ ስራዎች፣ የኬንያ የእንፋሎት እና የፀሐይ ኃይል ኢንሼቲቮች እንዲሁም የሞሮኮ ኑር ኦውርዛዛቴ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አረንጓዴ ልማት ሊሆን የሚችል ብቻ ሳይሆን በተጨባጭ የሚሳካ መሆኑን አፍሪካ ማረጋገጫ እንደሆነች በግልጽ የሚያመላክት ነው። አፍሪካ ከዓለም ዋንኛ በካይ ጋዝ ለቃቂ ሀገራት ገንዘብ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ሀገር በቀል የፋይናንስ እና ሀብት ማሰባሰብ አቅማቸውን የበለጠ ማሳደግ ይጠበቅባታል። የአዲስ አበባው ጉባኤም የአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ አቅርቦታቸውን እንዲጨምሩ ጥሪ የሚቀርብበት ነው። አፍሪካውያን እንደ አረንጓዴ አሻራ ያሉ ከንግግር ያለፉ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን በመተግበር አይበገሬ አቅም ሊገነቡ ይገባል። የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ሀገር በቀል የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄዎችን ከዓለም አቀፍ አጋርነት ጋር ከማዛመድ አኳያ ያላው ሚና ወሳኝ የሚባል ነው። ጉባኤው አፍሪካ ከአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ትርክት ወደ መፍትሄ አፍላቂነት እና የግንባር ቀደም ሚና አበርካችነት ለመሸጋገር እንደ መስፈንጠሪያ የሚያገለግል ትልቅ እድል ነው። የአዲስ አበባው ጉባኤ ከስብስባ ባለፈ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ቆርጣ ለተነሳችበት የተግባር ምላሽ ጉዞ እና የዓለም አቀፍ ተጠያቂነት መረጋገጥ የጋራ ትግል ውስጥ ትልቅ እጥፋት ሊሆን ይችላል።
በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የአንድ ሀገር የመልማት እና የማደግ ፍላጎት ሊገደብ አይገባም - አንቶኒዮ ጉቴሬዝ
Aug 5, 2025 737
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 28/2017(ኢዜአ)፦መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የአንድን ሀገር የመልማት እና የማደግ መብት በፍጹም መወሰን የለበትም ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ገለጹ። ሶስተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ኮንፍረንስ ዛሬ በተርኪሚኒስታን መካሄድ ጀምሯል። በኮንፍረንሱ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ፣እስያ፣አውሮፓ እና ደቡብ አሜሪካ የሚገኙ 32 ሀገራት ተሳታፊ ሆነዋል። ከተሳታፊዎቹ ሀገራት መካከል 16 ከአፍሪካ ናቸው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በኮንፍረንሱ ላይ ባደረጉት ንግግር የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ያሉባቸውን የልማት፣የኢኮኖሚ እና የእድገት ፈተናዎችን አንስተዋል። በማደግ ላይ የሚገኙ የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የመልማት አቅማቸው ባሉበት መልክዐ ምድራዊ ስፍራ ምክንያት ሊገደብ እንደማይገባ አመልክተዋል። ዋና ፀሐፊው የባህር በር የሌላቸው ሀገራት የዓለምን ሰባት በመቶ ህዝብ የያዙ ቢሆንም በዓለም ኢኮኖሚና ንግድ ውስጥ ያላቸው ድርሻ ከአንድ ፐርሰንት ጥቂት ሻገር ያለ መሆኑን ገልጸው ይህ ትልቅ ኢ-ፍትሃዊነት ነው ሲሉ ተናግረዋል። በተጨማሪም ሀገራቱ ለአየር ንብረት ለውጥ ያላቸው ድርሻ ዝቅተኛ ቢሆንም የጉዳቱ ዋንኛ ሰለባ መሆናቸውን አንስተዋል። የዓለም ማህበረሰብ ሀገራቱ በዓለም ኢኮኖሚ እና የንግድ ስርዓት ውስጥ ያላቸው ድርሻ እንዲያድግ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የንግድ እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ እንዲጨምር የሚያስችል መዋቅራዊ ለውጥ ያሻል ያሉት ዋና ፀሐፊው፥ ይህም ሀገራት ጥሬ ምርቶችን ከመላክ ከፍተኛ እሴት ያለው ምርት ወደ ማምረት እንዲሸጋገሩ ያደርጋል ነው ያሉት። የባለብዙ ወገን የልማት ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት አነስተኛ ወለድ ያለው የፋይናንስ አቅርቦት ለሀገራት ተደራሽ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ከትስስር ጋር በተያያዘ የሚገጥማቸውን የመሰረተ ልማት እና መዋቅራዊ ችግሮች መፍታት እንደሚገባ አመልክተዋል። ለዚህም ድንበር ተሻጋሪ አሰራሮችን ማቅለል፣የተለያዩ የመመዘኛ ደረጃዎችን ማጣጣም እንዲሁም የተሳለጠ ንግድና ትራንዚት እንዲኖር የሚያስችሉ የህግ ማዕቀፎችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ነው ያነሱት። ጉቴሬዝ በመሰረተ ልማት መጠነ ሰፊ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ ይገባል ያሉ ሲሆን የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት የማይበገር የትራንስፖርት መተላለፊያ መስመር፣ ድንበር ተሻጋሪ የእርስ በእርስ የኢነርጂ ትስስር፣ ሰፊ የአየር ትስስር እና በቴክኖሎጂ የታገዙ የሎጅስቲክስ አውታሮች እንደሚያስፈልጋቸው አስገንዝበዋል። ሀገራቱ ያለባቸውን የመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እክሎች ምላሽ ለመስጠት ፍትሃዊ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትን ማስፈን እንዳለባቸው አሳስበዋል። ኮንፈረንሱ ላይ ኢትዮጵያ እና የባህር በር የሌላቸው ሌሎች ሀገራት በዓለም የንግድ ስርዓት ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ በትስስር፣ በፍትሃዊ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነት እና ዓለም አቀፍ ትብብር እንዲያድግ ግፊት እንደሚያደርጉ ተመላክቷል። ሶስተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ የሚገኙ ሀገራት ኮንፍረንስ እስከ ነሐሴ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
ሐተታዎች
አስም-የበርካቶች ሰቀቀን …
Aug 28, 2025 67
በወቅትና የአየር ሁኔታ ሳይገደብ የበርካቶች ስቃይ የሆነውን አስም እንዴት ማከም ይቻላል…? የድንገተኛ እና ጽኑ ህሙማን ሐኪም ዶክተር ፍጹም አሸብር ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ለአስም ስለሚያጋልጡ መንስኤዎች፣ ምልክቶች፣ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄና ሕክምናው አብራርተዋል። • አስም ምንድን ነው? እንደ ዶክተር ፍጹም ገለጻ፤ አስም ለረጅም ጊዜ የሚኖር የመተንፈሻ አካላት ህመም ነው። የመተንፈሻ አካላት በቀላሉ፣ በተለያየ ሁኔታና መጠን መዘጋት ሲያጋጥም አስም ይባላል። • የአስም ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው? የትንፋሽ ማጠር፣ የደረት መጨናነቅ እና ሳል ከአስም ምልክቶች መካከል መሆናቸውን ያነሱት የሕክምና ባለሙያው፤ በአብዛኛው ምልክቶቹ በሌሊት ወይም በማለዳ እንደሚባባሱ ገልጸዋል። • የአስም ዓይነቶች 1. የአለርጂ አስም፡- ይህ የአስም ዓይነት በአለርጂዎች የሚቀሰቀስ መሆኑን ገልጸው፤ ለምሳሌ አቧራ፣ የአበባ ዱቄት (ዘር) ብናኝ፣ የእንስሳት ፍግ ሽታዎች አጋላጭ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። 2. አለርጂ ያልሆነ አስም፡- ይህ ደግሞ በኢንፌክሽን፣ በቀዝቃዛ አየር እንዲሁም በተበከለ አየር የሚነሳ የአስም ዓይነት መሆኑን ነው ያስረዱት። 3. በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ምክንያት የሚመጣ አስም፡- አካላዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት እንዲሁም ከሥራ በኋላ የሚከሰት የአስም ዓይነት መሆኑን ያስረዳሉ። 4. ከሥራ ጋር የተያያዘ አስም፡- በሥራ ቦታ ተጋላጭነት ምክንያት የሚቀሰቀስ የአስም ህመም ዓይነት መሆኑን ገልጸዋል። 5. ከባድ የአስም በሽታ፡- ይህኛው የአስም ህመም ዓይነት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ እና ባብዛኛው ባዮሎጂካል ሕክምናን የሚፈልግ መሆኑን አስረድተዋል። • ለአስም ህመም አጋላጭ ወይም ለህመሙ መባባስ መንስኤዎቹ ምንድን ናቸው? አለርጂዎች (የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን፣ የአየር ብክለት፣ ጭስ)፤ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ፣ ጭንቀት እንዲሁም የጄኔቲክ ቅድመ-ዝንባሌ ለአስም ህመም ከሚያጋልጡ እና ህመሙን ከሚያባብሱ ምክንያቶች መካከል መሆናቸውን ዶክተር ፍፁም ገልጸዋል። • አስም ያለባቸው ሰዎች ምን ይነት ጥንቃቄ ያድርጉ? ከአቧራ፣ ጭስ፣ አለርጂዎች መራቅና መጠንቀቅ፤ በኢንፍሉዌንዛ እና በኒሞኮካል ክትባቶች ወቅታዊ ክትባቶችን መውሰድ፤ በቀዝቃዛ የአየር ሁኔታ ወቅት ሙቀት የሚሰጡ ልብሶችን መልበስ፤ ጥሩ እንቅልፍ መተኛት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ፣ የተመጣጠነ አመጋገብን ማዘውተር እና መሰል ተግባራት የአስም ህመም እንዳይባባስ ያግዛሉ ብለዋል ባለሙያው። • ሕክምናውስ ምንድን ነው? የአስም ህመም የማስታገሻ እና የመቆጣጠሪያ (የረዥም ጊዜ) ሕክምናዎች እንዳሉት ያስታወቁት ባለሙያው እንደ ህመሙ ሁኔታ ስለሚወሰን ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ እንደሚገባ መክረዋል። በተለይም ምልክቶቹ በተባባሱበት ወቅት ከፍተኛ የአየር ትቦ መዘጋት ደረጃ ላይ እንዳይደርስ በጊዜ ሕክምናውን ማግኘት አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አንስተዋል።
አሸንዳ- የፍቅርና የሰላም አጀንዳ
Aug 23, 2025 372
በአማረ ኢታይ የሴቶች በተለይም የልጃገረዶች በዓል መሆኑ የሚነገርለት የአሸንዳ በዓል ለማክበር አመቱ እስከሚደርስ ድረስ በጉጉትና በናፍቆት ይጠበቃል። አሸንዳ ይዋቡበታል፣ ቁንጅና ጎልቶ ይወጣበታል፣ ልጃገረዶችና ሴቶች ተሰባስበው የሚያዜሙበት፣ በስጦታ ጭምር የሚታጀብ ልዩ እና ውብ የአደባባይ በዓል ነው። የአሸንዳ በዓል ሲቃረብ በተለይ ልጃገረዶች ቀደም ብለው የመዋቢያ ጌጣጌጦችንና አልባሳትን አዘጋጅተው የበዓሉን መድረስ ይጠባበቃሉ። እለቱም ሲደርስ በተለየ ሁኔታ ተውበውና ደምቀው ከበሮ ይዘውና በጣእመ ዜማ ታጅበው ወደ አደባባይ በመውጣት ያከብሩታል። በዚህም መሰረት ትግራይ የአሸንዳ በዓል በየዓመቱ ከነሃሴ 16 ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በደማቅ ስነ ስርአት ይከበራል። እለቱ የልጃገረዶች የነፃነት ቀንም በመሆኑ የቤተሰብ፣ የዘመድ አዝማድ ቁጣ እና ይህን አድርጊ ይህን አታድርጊ የሚል ትእዛዝ እና ጫና አይኖርም። በመሆኑም አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ያነገበ በመሆኑ ከልጅ እስከ አዋቂ በየአመቱ በጉጉት የሚጠበቅ ደማቅ በዓል ነው። የአሸንዳ ልጆች ከበዓሉ ዋዜማ ጅማሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ በየሰፈራቸው በቡድን በቡድን ተሰባስበው የሚጫወቱበት በመሆኑም የህብረት፣ የፍቅር፣ የሰላምና የአብሮነት ማሳያ ተደርጎም ይወሰዳል። ወላጆቻቸው አነስተኛ ገቢ ያላቸው ልጃገረዶችም ከእኩዮቻቸው፣ ከዘመድ አዝማድ እና ከጎረቤቶቻቸው የመዋቢያ ጌጣጌጦችን፣ አልባሳትና ሌሎች ቁሶችን ወስደው በዓሉን በደስታ የሚያሳልፉ ይሆናል። በዚህም መሰረት በዓሉ የመረዳዳት፣ የትብብርና ችግርን በመተጋገዝ ማለፍ እንደሚቻል የሚያመላክት ልዩ በዓል ነው። በዚሁ መሰረት የ2017 ዓ.ም የአሸንዳ በዓል በደማቅ ስነ ስርአት በመከበር ላይ ይገኛል። የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች፣ በርካታ ቱሪስቶች ልጃገረዶችና ሌሎችም የበዓሉ ታዳሚዎች በተገኙበት በመከበር ላይ ነው። በክብር እንግድነት በመገኘት ንግግር ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፤ ኢትዮጵያ በርካታ ውብ የሆኑ መገለጫዎች ያሏት ሀገር በመሆኗ አጉልተንና ለዓለም አስተዋውቀን የውበታችን ማሳያ እና የሃብት ምንጭ ጭምር ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል። የአሸንዳ በዓልን እሴት በመጠበቅ ለትውልድ ለማስተላለፍ ተቀናጅተን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የሚከበሩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን በማክበር ጠብቆ ማዝለቁ እንዳለ ሆኖ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን የማልማትና ታሪካዊ ቅርሶችን መጠበቅም ትኩረታችን ይሆናል ሲሉ ተናግረዋል። በመጨረሻም የአሸንዳ በዓልን በድምቀት እያከበረ ለሚገኘው ለመላው የትግራይን ህዝብ በተለይም ለልጃገረዶች የሰላምና የፍቅር በዓል እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል። "የአሸንዳ በዓልን ማስዋብና ማድመቅ ለሰላምና ለአንድነት ያለንን መልካም ፍላጎትና ምኞት ማሳያ ነው። ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና እንዲለማ እንሰራለን።" በማለት መልእክታቸውን ያጋሩት ደግሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ ናቸው። በጊዜያዊ አስተዳደሩ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አፅበሃ ገብረእግዛብሄር በበኩላቸው፣ ባህላዊ ይዘት ያለው የአሸንዳ በዓል ሳይበረዝ ትውፊቱን ጠብቆ እንዲቀጥል የክልልና የፌዴራል መንግስታት በጋራ እንሰራለን ብለዋል። በመቀሌ ከተማ እየተከበረ ባለው የአሸንዳ በዓል ከባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ሸዊት ሻንካ በተጨማሪ የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)፣ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና ሌሎችም ታድመዋል። አሸንዳ - የነፃነት፣ የፍቅርና የሰላም አጀንዳ ሆኖ መከበሩንም ቀጥሏል።
በሥራ ፈጠራ የስኬት ጉዞ የጀመረው ወጣት ተሞክሮ
Aug 22, 2025 339
(በያንተስራ ወጋየሁ - ከዲላ ኢዜአ ቅርንጫፍ) አንዳንዴ መዳረሻን የሚያሳምረው መነሻችን ነው ሲባል ይደመጣል።መነሻው ጥሩ ከሆነ ኋላ ለሚገኘው ስኬት መደላድል ይሆናል ለማለት ነው። ነገን አርቆ በማሰብና በማለም መስራት የህይወት ጉዞን ቀናና ስኬታማ ለማድረግ ጠቀሜታው የጎላ ነው። የሚገጥም ፈተናን እያሰቡ ወደኋላ ከማለት ይልቅ መፍትሄ በመፈለግ ወደስራ የገቡ ስኬት ሲያስመዘግቡ ይታያሉ። በዚህም ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎችም ወጣቶች ሲተርፉ ይስተዋላል። በፈተና ወደኋላ ሳይል ከችግሩ የሚወጣበትን መንገድ በመፈለግ ስኬት ማስመዝገብ የጀመረው የወናጎ ከተማ ወጣት ኤፍሬም ጴጥሮስ ለእዚህ አንድ ማሳያ ነው። ወጣቱ በከተማው የቱቱፈላ ቀበሌ ነዋሪ ነው። በ2015 ዓ.ም በ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ያመጣው ውጤት ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የሚያስገባ አልነበረም። በዚህ ምክንያት ሁለት ዓመታተን እንዲሁ ያለስራ አባክኗል። ያለሥራና ያለትምህርት ባሳለፋቸው ሁለት ዓመታት ድብርት ውስጥ ገብቶ እንደነበር ያስታወሰው ወጣት ኤፍሬም በዚህ ሁኔታ ግን ህይወቱን መቀጠል አልፈለገም። በዙሪያው ለሀብት ምንጭ የሚሆኑ ነገሮችን ትኩረት ሰጥቶ ማሰላሰል ጀመረ። በወናጎ ከተማ ራሱን ከመለወጥ ባለፈ የአካባቢውን ማህበረሰብ መጥቀም የሚችልባቸውን የሥራ አማራጮችን ማየቱን ቀጠለ። በዚህ ወቅት ነበር በአዲስ እሳቤ የተጀመረውና ብዙዎች በስፋት በመሳተፍ ተጠቃሚ እየሆኑበት ያለው የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ቀልቡን የገዛው። ይህ ሀገራዊ ኢንሼቲቭ ማህበረሰቡ ያለውን ልምድ የበለጠ በማስፋትና በማዘመን ተጠቃሚ እያደረገው በመምጣቱ የእሱንም ችግር ሊፈታ እንደሚችል ወጣቱ በማመኑ ቀዳሚ ትኩረት ያደረገው የዶሮ እርባታ ሥራ ላይ ነው። መንግስት ለማህበረሰቡ የዶሮ ጫጩቶችን በብዛት ማሰራጨት ተከትሎ ብዙች በዶሮ እርባታ ሥራ ተሰማርተዋል። የወናጎ ከተማ ነዋሪዎችም በዘርፉ ለመሰማራት ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት የዶሮ ጫጩቶችን በብዛት ሲረከቡ በየዕለቱ ማየቱ በውስጡ አንድ ነገር አጫረበት። በከተማው ለብዙ ሰዎች ለዶሮ እርባታ የሚሆን በቂ ስፍራ ማግኘት አዳጋች መሆኑ ለአምራቾች ትልቅ ፈተና ነው። ይህን የተረዳው ወጣቱ ለዚህ ችግር መፍትሄ ሊሆን የሚችል ነገር ቢሰራ አንድም ለራሱ ሥራ መፍጠር ነው፤ በሌላ ቡኩል የነዋሪዎችን ችግር መፍታት መሆኑን አሰበ። በአካባቢው ካሉ ግብአቶች በቀላል ወጪ ለማህብረሰቡ ይጠቅማል ያለውን ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት ለመስራት ወሰነ። ጉዳዩን ከራሱና ከሌሎች ጋርም መከረበት። በእዚህም ወደስራው ለመግባት የሚያስችል ገንቢ ምክረ ሀሳብ አገኘ። ሀሳቡ አዲስና ለነዋሪውም የሚሰጠው ጥቅም የጎላ መሆኑ ደግሞ ይበልጥ አበረታታው። ይህም ተጨማሪ ብርታት ሆኖት ሀሳቡን ወደድርጊት በመቀየር "ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት" በመስራት ለሽያጭ ማቅረብ ጀመረ። ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤቱ በጥቂት ቦታ በአንድ ጊዜ 120 የዶሮ ጫጩቶችን ለማርባት የሚያስችልና ሰፊ ቦታ የማይዝ መሆኑም በብዙዎች ዘንድ ተመራጭ እድርጎታል። ወጣት ኤፍሬም በወናጎ ከተማ ያለውን የቦታ ችግር ለመፍታት በአካባቢው ያለን ግብአት ተጠቅሞ የሰራው ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት ዛሬ ከጌዴኦ ዞንና ወናጎ ከተማ ባለፈ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደረጃ በብዙዎች ዘንድ ተፈላጊ እየሆነ መጥቷል። ከስኬቶቹ መካካል በዚህ ሥራው በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ ተስፋ ሰጪ ለውጥ እያሳየ ነው። የራሱን ሥራ ከፈጠረ ከአንድ ዓመት ያነሰ ጊዜ ቢሆነውም ከራሱና ከቤተሰቦቹ አልፎ ለሦስት የአካባቢው ወጣቶችም የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል። በወር ከአራት በላይ የተንቀሳቃሽ ዶሮ ቤቶችን በመሸጥ ከ100 ሺህ ብር በላይ ገቢ እንደሚያገኝ የሚናገረው ወጣቱ የዶሮ ቤት ሥራውም በህይወቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ለውጥ እንዲያመጣና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱን እንዳሳደገው ይናገራል። በዚህም ሰርቶ ለመለወጥ ያለው ፍላጎት መነሳሳቱን የገለጸው ወጣቱ ጎን ለጎን የዶሮ እርባታ ሥራ ጀመረ። ተንቀሰቀሽ የዶሮ ቤት አዘገጅቶ ከመሸጥ ባለፈ ለሌሎች አርቢዎች ማስተማሪያ ይሆናል በሚል የ45 ቀን የእንቁላል ጣይ የዶሮ ጫጩቶችን በማርባት ለአካባቢ ማህበረሰብ እያቀረበ ይገኛል። ይህም ሥራውን በመጠንና በአይነት ለማስፋትና ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት አስችሎታል። የለውጡ ምክንያት "በአጭር ጊዜ ላሳየሁት ለውጥ ምክንያቱ ለሥራ ያለኝ ተነሳሽነት ነው" የሚለው ወጣቱ የተጠናከረ የገበያ ትስስርም እንዳለው ተናግሯል። በሚገጥም ችግር ተስፋ መቁረጥ መፍትሄ እንደማይሆን ለሌሎች ወጣቶች ይመክራል። ከዚያ ይልቅ በአካባቢ ያለን ሀብት ለልማት በማዋል ተጠቃሚነትን ለማሳደግ መስራት እንደሚገባ ነው የገለጸው። በተለይ ኑሮ ለውጥ ለማምጣት በሀገራዊ ኢንሼቲቮች በመሳተፍ ተጠቃሚ ለመሆን ተግቶ መስራት ይገባል ባይ ነው። የወጣቱን የዶሮ ቤት በመጠቀም በዶሮ እርባታ ሥራ ከተሰማሩ የወናጎ ከተማ ወጣቶች መካከል ወጣት አማኑኤል ቦጋለ አንዱ ነው። ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤቱ በውስን ስፍራ ዶሮ የማርባት ፍላጎቱን አሳክቶለታል። ሦስት ካሬ ብቻ የሚይዘውን የዶሮ ቤት በ20 ሺህ ብር በመግዛት በ120 የዶሮ ጫጩቶች ሥራውን ጀምሮ እያከናወነ ይገኛል። በአሁኑ ወቅትም ከራሱ ፍጆታ ባለፈ እንቁላል በመሸጥ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱን ነው የተናገረው። የዶሮ ቤቱ የመመገቢያ፣ የማደሪያና ኩስ መጥሪግያ በዘመናዊ መንገድ የተዘጋጀለት መሆኑ ስራውን በቀላሉ ለማከናውን እንዳስቻለውም ገልጿል። የዶሮ ቤቱ እሱን ጨምሮ ለብዙዎች ከቦታ እጥረት ጋር በተያያዘ የነበረባቸውን ችግር እንደፈታ የገለጸው ወጣቱ፣ በሌማት ትሩፋት የተጀመረው የዶሮ እርባታ ሥራ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ተናግሯል። ይህን የሌማት ትሩፋት ሥራ የሚያጠናክሩ የፈጠራ ሥራዎች ደግሞ ተጠቃሚነትን ይበልጥ ስለሚያሳድጉ መስፋፋት እንዳለባቸውም ነው የተናገረው። በወናጎ ከተማ አስተዳደር ግብርና ዩኒት የእንስሳት ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሮ ፀደይ አጋደ በከተማዋ ከፍተኛ የሰዎች ጥግግት እንዳለ ያነሳሉ። ይሁን እንጂ የአካባቢውን ሀብቶች በመጠቀም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ስራዎች ብዙዎች ተጠቃሚ እየሆኑና ህይወታቸውን እየለወጡ መጥተዋል። ነዋሪውም በዶሮ እርባታ ተሰማርቶ ተጠቃሚ ለመሆን ያለው ፍላጎት ከፍተኛ ነው። የሌማት ትሩፋት ኢኒሼቲቭን ተከትሎ በዶሮ እርባታ የሚሰማሩ ሰዎች ቁጥር ቢጨምርም የቦታ እጥረት ፈተና ሆኖ መቆየቱን ያነሳሉ። የህብረተሰቡን የቦታ ጥያቄ መፍታት ለአስተዳደሩ መሰረታዊ ተግዳሮት እንደነበር አስታውሰው፤ ወጣት ኤፍሬም በአካባቢ ከሚገኝ ግብዓት ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤት ስርቶ ለሽያጭ ማቅረቡ ችግሩን እያቀለለው መሆኑን ይናገራሉ። ወይዘሮ ፀደይ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በከተመው በሦስት የዶሮ መንድሮች የዶሮ እርባታ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል። በዚህም 14 በማህበር የተደራጁ እና ከ80 በላይ በግል የተሰማሩ ዶሮ አርቢዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው። የልማት ሥራው እንቁላልና ዶሮ ለማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እያስቻለ ነው። በወጣቱ የተሰራው ተንቀሳቃሽ የዶሮ ቤትም ከቦታ ጥበት ጋር በተያያዘ ከነዋሪዎች ሲነሳ የነበረውን ጥያቄ እየፈታ መሆኑን አስተባባሪዋ ይገልጻሉ። እንደወጣት ኤፍሬም የዜጎችን ችግር የሚፈቱና በመንግስት የሚከናወኑ የልማት ተግባራትን የሚያግዙ ፈጠራ የታከለባቸው ሥራዎች ልማቱ የበለጠ ስለሚያጠናክሩ የሚደገፉና የሚበረታቱ መሆናቸውን ነው የገለጹት። በየአካባቢው ያልተነኩ ሀብቶች አሉ። ዋናው ነገር ግን እነዚህን ሀብቶች እንዴት ወድልማት በመቀየር ተጠቃሚ መሆን ይቻላል የሚለው ነው። በተለይ ወጣቶች ሥራ የለም በሚል ምክንያት የማይተካ ጊዜን ያለአግባብ ማሳለፍ አይገባም። ህገወጥ ስደትን ምርጫ ማድረግም አግባብ እንዳልሆነ የወጣት ኤፍሬም ተሞክሮ እንድ ማሳያ ነው። መንግስት የዜጎችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የተለያዩ ኢኒሸቲቮችን ቀርጾ ወደተግባር አስገብቷል። በእነዚህ ኢኒሼቲቮች መሳተፍና እንዴት ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ ቆም ብሎ ማሰብ ብቻ ነው ከእነሱ የሚጠበቀው። ያኔ መዳረሻቸውን አርቀው ማለም ይጀምራሉ። መነሻቸው መሰረት ከያዘ መዳረሻቸውን ማሳመር ይችላሉና ከወናጎ ከተማ ወጣት ኤፍሬም የስኬት ጉዞ ትምህርት መውሰድ ይገባል።
ልምድን ያዘመነው የሌማት ትሩፋት ለአርሶ አደሩ ምግብም ገንዘብም ሆኗል
Aug 20, 2025 362
(በመንበረ ገበየሁ - ከኢዜአ ሀዋሳ ቅርንጫፍ) የሌማት ትሩፋት በ2015 ዓ.ም ጥቅምት ወር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በአርባ ምንጭ ከተማ ይፋ ያደረጉት መርሀግብር ነው፡፡ በምግብ ራስን በመቻል የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥም ያለመ ነው። መርሀግብሩ በዋናነት የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ልማት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ተኩረት አድርጓል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንደገለጹት መርሃ ግብሩ አርሶና አርብቶ አደሩን የሚያገናኝ ድልድይ በመሆን በልቶ ከማደር በላይ ከምግብ እጥረት ጋር የተያያዘ ታሪካችንን የሚቀይር ነው፡፡ ለመርሀግብሩ ስኬታማነትም መንግስት ዝርዝር ጥናት አድርጎና እቅድ አውጥቶ ወደ ስራ ከገባ ሦስት ዓመታትን እያስቆጠረ ነው፡፡ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) እንደሚሉት መርሃ ግብሩ የምግብ ሥርአትን በማሻሻል፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና የሥራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚው እንዲነቃቃ እያገዘ ነው። ከዚህ በተጨማሪ የእንስሳት ሃብት ልማቱን ውጤት በአምስት እጥፍ እንዳሳደገው ነው የገለጹት። ዘርፉን በተያዘው በጀት ዓመት ለማሳደግ ከ160 ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችን የማሰራጨትና 5 ሚሊዮን የእንሰሳት ዝርያ የማሻሻል ሥራዎች ይሰራሉ። ከዚህ ጎን ለጎን 17 ቢሊዮን ሊትር ወተት፣ 12 ቢሊዮን እንቁላል ለማምረትና የዓሣ እና የማር ምርትንም ለማስፋት ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ይናገራሉ። መርሀግብሩ የክልሎችን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ አድርጎ የተቀረጸ በመሆኑ በሲዳማ ክልልም መርሀግብሩን ውጤታማ ለማድረግ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ በክልሉ በሰባት ፓኬጆች በተጀመረው ሥራ የእንስሳት ሃብት ምርታማነትን አሳድጓል። የዓሣ ልማትን ከሀዋሳ ሐይቅ በተጨማሪ በተለያዩ የአሣ መንደሮችና ኩሬዎች መተግበራቸው በሃገር ደረጃ ምሳሌ ሆነዋል ብለዋል ፍቅሩ (ዶ/ር)፡፡ እንደ ሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ የሌማት ትሩፋት ኢኒሺየቲቭን ተከትሎ የእንስሳት ሀብት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል። በዚህም የመኖ እጥረት እየተስተዋለ ቢመጣም መንግስት ችግሩን ለመፍታት አማራጭ የመኖ ልማት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም በተያዘው በጀት ዓመት ከ1 ሚሊዮን 750 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተሻሻለ መኖ በማልማት ከ263 ሺህ 500 ኩንታል በላይ የመኖ ዘር ለማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። በአርብቶ አደሩ አካባቢ የሚገኙ ሰፋፊ የግጦሽ መሬቶችን ከማልማት በተጨማሪ የተመጣጠነ መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን የማስፋት ሥራም እየተከናወነ ነው፡፡ የመኖ ልማት ሥራው የእንስሳት ሃብት ልማቱን ምርታማነት ከመጨመር ባሻገር ከምርቱ ጋር ያልተጣጣመውን የእንስሳት ተዋጽኦ ዋጋ መናር የሚያረጋጋና ለአካባቢ ጥበቃ ስራም ጉልህ አበርክቶ ይኖረዋል። ''ዶሮ ቤት ከሌላት ጅግራ ነች'' በሚል መርህ ሞዴል የዶሮ ቤቶችን ግንባታ በማከናወንም ክልሉ በሀገር ደረጃ ቀዳሚ ሲሆን ስራው በዶሮ እርባታው ዘርፍ ለተገኘው ውጤት ጉልህ አበርክቶ አለው፡፡ ልክ እንደቤተሰብ አባል በሰላምታ ልውውጥ ወቅት የእንስሳቱን ጤናንም ለሚጠይቀው የሲዳማ ህዝብ እንስሳት ምግቡም፣ ልብሱም፣ መጦሪያና ገንዘቡም ጭምር ነው፡፡ የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ደግሞይህን የህብረተሰቡን ከእንስሳት ጋር ያለውን ቁርኝት ያጠናከረ፣ ከዘርፉ የሚያገኘውን ጥቅም ለማሳደግ እድል የፈጠረ ነው፡፡ የክልሉ እንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ተክሌ ጆምባ እንደሚናገሩት ደግሞ እንስሳት ለክልሉ ህዝብ " በህይወት ያለ ባንክ" ነው፡፡ በዚህም የዶሮ፣ የወተት፣ ዓሣ፣ ንብና ሃር ትልን ጨምሮ በሰባት ፓኬጆች ከ2 ሺህ 600 በላይ መንደሮችን በማደራጀት እያንዳንዱ አርሶ አደር እንዲሳተፍ በመደረጉ መርሃ ግብሩ ብዙዎችን ተጠቃሚ እያደረገና ህይወታቸውን እየቀየረ ነው፡፡ እንደ አቶ ተክሌ ገለጻ በሲዳማ ክልል በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በመርሃ ግብሩ ከ500 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ መርሀግብሩ ከተጀመረ ጀምሮ በእንሰሳት ሃብት ልማቱ ምርታማነት ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችም አመርቂ ናቸው፡፡ መርሀግብሩ ሲጀመር ተሰራጭቶ የነበረውን 857 ሺህ የአንድ ቀን ጫጩት ዘንድሮ ወደ 20 ሚሊዮን ማሳደግ ተችሏል። የእንስሳት ዝርያን ማሻሻል በመቻሉም ለይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና ለአዲስ አበባ ገበያ በየሦስት ቀን እስከ 4ሺህ 500 ሊትር ወተት የማቅረብ አቅም መፈጠሩን አቶ ተክሌ ይገልጻሉ፡፡ በተያዘው በጀት ዓመትም ከ260 ሺህ በላይ ከብቶችን ዝርያ የማሻሻል፣ 158 ሺህ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን ለማሰራጨት ታቅዶ ወደስራ ተገብቷል፡፡ በክልሉ በዶሮ ልማትና በሌሎችም ፓኬጆች የተጀመሩ ሥራዎችን ምርታማነት የማሳደግ ሥራም ትኩረት ተሰጥቶታል። በዚህም የሌማት ትሩፋት መርሀግብር የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ አቅም እያሳደገ፣ የምግብ ሉአላዊነቱን እያረጋገጠና የሥራ ዕድልም እየፈጠረ መጥቷል ማለት ይቻላል። በሸበዲኖ ወረዳ የጣራ ሜሳ ቀበሌ ነዋሪው አርሶ አደር ካሳ ካያሞ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ በወተት ላሞችና ዶሮ እርባታ፣ በዓሣና ንብ ማነብ ትኩረት አድርገው እየሰሩ ነው፡፡ የእንስሳት ልማት እንደ ልጅ እንክብካቤን የሚፈልግ በመሆኑ የመኖ ልማት ሥራው ላይ እየተሳተፉ መሆኑንም ገልጸዋል። የእንስሳት ተረፈ ምርትን ለማዳበሪያነት መጠቀማቸው ለመስኖ ልማት ምርታማነት እያገዛቸው ነው፡፡ የሌማት ትሩፋትም የእሳቸውን ጨምሮ የአካባቢውን አርሶ አደሩ ኢኮኖሚ ከመደገፍ ባለፈ የአናኗር ዘይቤያቸውን እየቀየረው ነው፡፡ የበንሳ ወረዳዋ ሞዴል አርሶ አደር እቴነሽ ታዬ ከንብ ማነብ በተጨማሪ ዓሣና ዶሮ በማርባት የሌማት ትሩፋት መርሀግብር ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ በእንስሳት እርባታ የበነራቸውን ልምድ በሌማት ትሩፋት በማዘመን ይበልጥ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ የዓሣ ሃብት ልማትን ኩሬ አዘጋጅተው እያከናወኑ ይገኛሉ። በዘመናዊ ቀፎ የታገዘው የንብ እርበታ ሥራቸውም ከፍተኛ ገቢ እያስገኘላቸው ነው፡፡ ከላሞቻቸውና ከዶሮዎቻቸው የሚያገኙት ወተትና እንቁላል የአመጋገብ ሥርአታቸውን ቀይሮታል። ከዚያም ባለፈ በዓመት እስከ 40ሺህ ብር በማግኘት ኢኮኖሚያቸውን እየደጎሙ ነው። በሌማት ትሩፋት መርሀግብር ጋር የተደገፈው የእንስሳት ሃብት ልማት ሥራችን ከባህላችን ጋር የተሳሰረ በጠባብ መሬት ብዙ የምናተርፍበት ዘርፍ ነው ሲሉም አርሶ አደር እቴነሽ ገልጸዋል፡፡ በሲዳማ ክልል ደረጃ በህዳር ወር 2015 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የህይወት ባንካቸው ለሆነው የእንስሳት ሃብት ልማት የፈጠረውን ምቹ እድል ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እያደረገ ነው፡፡
ትንታኔዎች
የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት አንገብጋቢው ጉዳይ
Aug 6, 2025 731
የባህር በር ጉዳይ በሀገራት ዘንድ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ግዙፍ ኢኮኖሚና ሰፊ ህዝብ ላላቸው ሀገራት ሕልውና ጉዳይ ሆኗል። በቱርክሜኒስታን አዋዛ ከተማ ሶስተኛው ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራት ጉባዔ በመካሄድ ላይ ይገኛል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም በጉባኤው መክፈቻ ላይ ቁልፍ መልዕክት አስተላለፈዋል። ዋና ፀሐፊው ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በተለይም መልኩ እየተለዋወጠ ባለው ዓለም፤ በአየር ንብረት ለውጥና መሰል ተጽዕኖዎች ሳቢያ መልከ ብዙ ፈተና እንደተደቀነባቸው ገልጸዋል። በተለይ ለአንዳንዶቹ ህልውናቸውን እየተፈታተነ ስለመሆኑም አጽንኦት ሰጥተዋል። የዋና ጸሐፊው ንግግርም ፦ ዛሬ ከዚህ የተሰባሰብነው ለማንክደው አንድ ዕውነት ነው። መልክዓ ምድር መዳረሻን መወሰን የለበትም። ነገር ግን በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በላቲን አሜሪካና በአፍውሮፓ 32 ሀገራት ባህር በር ስለሌላቸው የማደግ ዕድላቸው ተገድቧል፤ ኢ-ፍትሃዊነትንም አስፍቷል። ሀገራችሁ አያሌ ተግዳሮቶች ተጋርጦባቸዋል። ዕድገታቸው እንዲወሰን፣ በከፍተኛ የወጪ ንግድ ትራንስፖርት እንዲበዘበዙና በዓለም ገበያ ተደራሽ እንዳይሆኑ ፈተና ገጥሟቸዋል። በርካቶች በጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት እንዲወሰኑ፣ ለተለዋዋጭ ዓለም አቀፍ ገበያ እንዲጋለጡ ብሎም በጠባብ ኢኮኖሚያዊ መሰረት እንዲታጠሩ አድርጓቸዋል። በሌላ በኩል የዕዳ ጫና ለመልከ ብዙና ዘላቂነት ላለው ችግር ዳረጓቸዋል። አንድ ሶስተኛው የዓለማችን ባህር በር አለባ ሀገራትም ለደህንነት እንዲጋለጡና የግጭት አዙሪት ችግር እንዲገጥማቸው ተገደዋል። ምንም እንኳን 7 በመቶው የዓላማችን ህዝብ ድርሻ ቢይዙም በዓለም ኢኮኖሚ አንድ በመቶ ብቻ ድርሻ ይዘዋል። ይህም ምንጊዜም ኢ-ፍትሃዊነትና መገለል ሁነኛ ማሳያ ነው። ይህ የኢ-ፍትሃዊነት መልክ ዘላለማዊ መሆን የለበትም። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በዓለም የፋይናንስና የንግድ መዋቅር ውስጥ ለከፍተኛ ችግር የተጋለጡ ናቸው። በበይነ-ዓለም ትስስር በገሀድ በሚታይበት የዛሬው የዓለም መልክ ስርዓታዊ መድሎና መገለል በይፋ የደረሰባቸው ሀገራት ናቸው። ይህም በብዙ ምክንያቶችም የቅኝ ግዛት አሻራ ምልክት ነው። በቅርብ ጊዜ ትውስታዎች እንኳን ከኮቪድ 19 እስከ አየር ንብረት ለውጥ ቀውሶች፣ ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል እስከ ግጭት እንዲሁም በጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ሳቢያ ባህር በር የሌላቸው ሀገራት ዘላቂ የልማት ግቦችን ዕውን ለማድረግ ተቸግረዋል። ይህ ጉባኤ ችግሮችን ከማንሳት ባሻግር መፍትሄዎች ላይ ማተኮር አለበት። የቀጣይ ዘመን የእድገት መሻት ጉዞን መቀየስ ብሎም ባህር በር አልባ ታዳጊ ሀገራትን የማልማት ዕድሎች በጋራ መግለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምክር ይገባል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም በዚህ ረገድ ከሀገራቱ ጎን የቆመ ነው። በቀጣይ አስርት ዓመታት በትብብር መሰራት ካለባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መዋቅራዊ ሽግግርን ማሳለጥ እና ኢኮኖሚያዊ ስብጥርን ማብዛት ላይ መተኮር ይገባል። ምክንያቱም እነዚህ ሀገራት በሰው ሃይል እና በተፈጥሮ ሀብት የታደሉ ቢሆንም በፋይናንስ እጥረትና በገበያ እጦት ይህን አቅም ተጠቅመው መልማት አልቻሉም። ወሳኝ የሆኑ እሴት ጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት፣ ሀገር ውስጥ ፈጠራዎችን ማጎልበት እንዲሁም ለቀጣናው ለትውልድ ትሩፋት የሚያቋድስ አካታች ልማትን ዕውን ማድረግ ይሻል። የሀገራቱን የገበያና የመልክዓ ምድር ተግዳሮቶችን ለማቅለል አንዱ መፍትሄ የዲጂታላይዜሸን ሽግግር ነው። በዲጂታል ምህዳር ተደራሽነት ለማቅለልም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስራዎች መጠንከር አለባቸው። የግል ዘርፉን ማጠናከርም ኢ-ፍትሃዊነትና ተደራሸነትን ችግርን ለማቅለል ያግዛል። ሀገራቱ በቋንቋ፣ በባህልና በጥበብ በጥልቅ የተቆራኙ ናቸው። በሀገራቱ መካከል ያለው የተቆራረጠ ሎጂስቲክስ፣ ያልተሳለጠ የድንበር ግብይት፣ የተሟላ መሰረተ ልማት አለመኖር በዓለም ገበያ ተወዳደሪና ተደራሽ ለመሆን አልቻሉም። በመሆኑም ድንበር ዘለል የሆኑ ትስስሮችን ማሳለጥ በተለይም ሀገራትን የሚያስተሳሰሩ ኮሪደሮችን መገንባት፣ የጭነት ሎጂስቲክስን ማሳለጥ፣ የሃይል እና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን መጨመር ያስፈልጋል። ይህን መንገድ በመከተል በቀጣናውና በዓለም ገበያ መግባት ብሎም ከጥሬ ዕቃ አቅራቢነት ወደ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ማቅረብ መሸጋገር ይቻላል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የንግድ ግብይት መልክን መለወጥ፣ የትብብርና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተቃኘ አካሄድ መከተል ይገባል። ዓለም አቀፍ የባለብዙ ወገን የፋይናንስ ተቋማትም የበይነ ሀገራት የድንበር ላይ ትስስርና የጋራ ልማት ላይ ተገቢውን የኢንቨስትመነት ልማት ፋይናንስ ማቅረብ ይገባቸዋል። ባህር በር የሌላቸው ሀገራት በቀጣናው ደረጃ ከተሰባሰቡ ልማትን ዕውን ማድረግ ያስችላልና። ባህር በር አልባ ሀገራት ምንም እንኳን ከዓለማችን ሀገራት የበካይ ጋዝ ልቀታቸው ለከ3 በመቶ ያነሱ ቢሆነም የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ ገፈት ቀማሾች ግን እንርሱ ናቸው። ከሰሃራ በርሃ መስፋፋት እስከ በረዶ የሚቀልጥባቸው ተራራማ ሀገራት፣ የኤስያ ሀገራት አስቸጋሪ የአየር ጸባይ ለውጥ፣ በከባድ ዝናብና አውሎንፋስ የሚመቱ የላቲን አሜሪካ ሀገራት ለዚህ ማሳያ ናቸው። የአየር ንብረት ለውጥ ባህር በር አልባ ሀገራትን እየበላቸው ነው። የአየር ንብረት ለውጥና ባህር በር አልባነት ተዳምሮ ዕድገታቸውን እንዲወሰን ለአንዳንዶቹም በህልውናቸው ላይ አደጋ ደቅኗል። በተባበሰው የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ሳቢያ በአንድ አዳር በሚደርስ የመሰረተ ልማት ውድመት የሀገራት ዓለም አቀፍ ንግድ ተሳትፎ አደጋ ውስጥ ይወድቃል። በመሆኑም ቃል የተገቡ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ መቋቋሚያ ፋየናንስ መተግበር፣ ተዕጽኖ የሚቋቋም መሰረተ ልማት መዘርጋት ይሻል” በማለት ነበር መልዕክታቸውን ያስተላለፉት። በአረንጓዴ ልማት፣ በፋይናንስ ማሰባሰብ፣ በብድር አቅርቦት እና ወለድ አያያዝና ትግበራ ጉዳይም ልብ መባል ያለበትን ጉዳይ ጠቅሰዋል። ባህር በር አልባ ሀገራት በጋራ ነጋቸውን ለማሳመርና ፈተናዎቻቸውን ለመሻገር በትብብር እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል። ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት ጥያቄዋን በይፋ ከገለጸች ውላ አድራለች፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የባህር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸው ይታወሳል።
ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሽግግር ለምን አስፈለጋት?
Jul 19, 2025 1107
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቲኒዮ ጉቴሬዝ አነሳሽነት እ.አ.አ 2021 የተመድ የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በኒው ዮርክ በበይነ መረብ አማራጭ ተካሄዷል። “የህዝቦች ጉባኤ” እና “የመፍትሄ ጉባኤ” የሚሉ ስያሜዎች የተሰጠው ጉባኤ ላይ ከ193 ሀገራት የተወጣጡ ከ51 ሺህ በላይ ሰዎች ተሳትፈውበታል። በምግብ ስርዓት ላይ የተዘጋጀ ይህ ታሪካዊ ጉባኤ ዓለም አቀፍ ሁነት ዋንኛ ግቡ የነበረው የተመድ አባል ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን እንዲያመጡ እና ስርዓተ ምግብን ከዘላቂ ልማት ግቦች በተለይም ከግብ ሁለት ረሃብን ማጥፋት ጋር ማስተሳሰር ነው። ጉባኤው በአምስት ዓበይት የትኩረት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ለሁሉም ዜጋ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ ተደራሽ ማድረግ፣ ከብክነት ወደ ዘላቂ የምግብ አጠቃቀም መሸጋገር፣ ተፈጥሮን ያማከለ የምግብ ምርማነትን ማሳደግ፣ እኩልነትን መሰረት ያደረገ የአኗኗር ሁኔታን ማጠናከር እና ለአደጋዎችና ጫናዎች የማይበገር ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ጉባኤው የተወያየባቸው ጉዳዮች ናቸው። ጉባኤው በወቅቱ አባል ሀገራት ሁሉን አቀፍ የምግብ ስርዓትን በመፍጠር የዘላቂ ልማት ግቦችን እንዲያሳኩ ጥሪ አቅርቧል። የተመድ የዓለም የምግብ ደህንነት ኮሚቴ የምግብ እና የስነ ምግብ ከፍተኛ የባለሙያዎች ፓናል የስርዓተ ምግብ አካሄድ ከባቢ አየር፣ ዜጎች፣ ግብአቶች፣ ሂደቶች፣ መሰረተ ልማቶችና ተቋማትን ጨምሮ ሁሉንም ተዋንያን ያሳተፈ መሆን እንዳለበት ያስቀምጣል። ስርዓተ ምግብ ምርት፣ ማቀነባበር፣ ስርጭት፣ ማዘጋጀት፣ መመገብ እና የተረፈ ምግብ አወጋገድን አቅፎ የያዘ እና ይህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ከባቢ አየር ላይ ቀጥተኛ ተጽእኖ ያለው ነው። የባለሙያዎች ፓናሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ዜጎች፣ ምድር፣ ብልጽግና፣ ሰላም እና አጋርነት ላይ ያውጠነጠነ መሆኑን ይገልጻል። ፓናሉ ይህን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ያመጣል ያላቸውን ስድስት ሀልዮታዊ ማዕቀፎችን ቀርጿል። ህይወት ያላቸው እና የቁስ አካላት ባህርያት፣ ከባቢ አየር የመጀመሪያው ነው። በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽንና መሰረተ ልማት ሲሆን ኢኮኖሚ እና ገበያ ሶስተኛውን ስፍራ ይይዛል። ፖለቲካ እና ተቋማዊ ሁኔታ፣ ማህበራዊ እና ባህላዊ ጉዳዮች እንዲሁም የስነ ሕዝብ ውቃሬ ሌሎች የምግብ ስርዓት ለውጥ አምጪ ምክንያቶች እንደሆኑ ተቀምጧል። ስድስቱ የምግብ ለውጥ አሳላጭ ሁኔታዎች ተፈጻሚ እና ውጤታማ የሚያደርጉ አራት ቁልፍ መስኮች እንዳሉም የባለሙያዎች ፓናሉ ያስቀምጣል። የምግብ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስርዓቶችን መደገፍ፣ የምግብ አቅርቦት ሰንሰለትን ማጠናከር፣ የዜጎችን የምግብ አጠቃቀም ባህሪያት ላይ ለውጥ ማምጣት እና የተመጣጠኑ ንጥረ ምግቦችን ብዝሃነት ማስፋት ቁልፍ የትኩረት ጉዳዮች ናቸው። የተቀመጡትን ማዕቀፎች፣ ለውጥን የመፍጠሪያ መንገዶች እና አስቻይ ሁኔታዎች ከፖሊሲ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደር ጋር በማቆራኘት የምግብ ስርዓት ላይ ለውጥ ማምጣት እንደሚገቡ ባለሙያዎቹ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ። የኢትዮጵያ የስርዓት ምግብ ራዕይ (EFS) መነሾም በስርዓተ ምግብ ጉባኤው እ.አ.አ በ2030 መሳካት አለባቸው ብሎ ያስቀመጣቸውን የስርዓተ ምግብ ግቦች እውን ለማድረግ ያሉ ፈተናዎች እና እድሎች ናቸው። እ.አ.አ በ2024 የወጣው የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ በጉባኤው የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት እና የጉባኤውን ምክረ ሀሳቦች ለመተግበር ቁርጠኛ እንደሆነች ይገልጻል። የኢትዮጵያ መንግስት እ.አ.አ ዲሴምበር 2020 የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ የአሰራር ሂደት ይፋ ያደረገ ሲሆን ሂደቱ እ.አ.አ ጃንዋሪ 2021 ተጀምሯል። የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ራዕይን በግልጽ ያስቀመጠ ነበር። በወቅቱ ሂደቱን ለማስጀመር የቀድሞ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን እና የቀድሞ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ የመሯቸው የከፍተኛ ደረጃ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ሰነዶችም ተቀርጸዋል። በስርዓት ምግብ ላይ ሁለት ብሄራዊ ምክክሮች የተደረጉ ሲሆን ምክክሮችን ተከትሎ የኢትዮጵያ ስርዓተ ምግብ ሂደት ይፋ ሆኗል። ምክክሮቹ የኢትዮጵያ ምግብ ስርዓት አሁናዊ ሁኔታ አና መጻኢ ሁኔታዎች፣ የኢትዮጵያን የምግብ ስርዓት የመለወጥ ጉዞ በሚል ርዕስ የተካሄዱ ናቸው። የስርዓተ ምግብ ሂደት ቀረጻው ላይ መንግስት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህረሰቦች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ተቋማት ያሉባቸው ከ120 በላይ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። ይፋ የሆነውም የስርዓተ ምግብ ሂደት ሰነድ እ.አ.አ በ2021 በጣልያን ሮም በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ላይ ቀርቦ አዎንታዊ ምላሾችን አግኝቷል። የስርዓተ ምግብ ሂደት ማዕቀፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ፣ ከ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ እንዲሁም ከሌሎች የፖሊሲ እና አሰራሮች ጋር የተጋመደ ነው። የኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ሁሉን አቀፍ ሪፖርት ኢትዮጵያ የስርዓተ ምግብ ለውጥ እና ሽግግር ያስፈለገባቸውን ምክንያቶች ያስቀምጣል። የምግብ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነት በሚፈለገው ደረጃ ማረጋገጥ አለመቻል፣ ፈጣን የህዝብ እድገት፣ የክትመት መጠን መስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳት እና የአየር ንብረት ለውጥ፣ እኩል ያልሆነ የዜጎች አኗኗር፣ ደካማ የምግብ ስርዓት መሰረት፣ ግብርናን ለኢኮኖሚ ያለውን ድርሻ ማሳደግ እና የምግብ ስርዓትን ከብሄራዊና ዓለም አቀፍ ግቦችን ጋር ማሰናሰን ማስፈለጉ የስርዓተ ምግብ ለውጡ መሰረታዊ ለውጥ መነሻ ናቸው። ኢትዮጵያ በስርዓተ ምግብ ሽግግር ውስጥ ስንዴን ጨምሮ በተለያዩ ሰብሎች ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የንጥረ ነገሮችን ብዝሃነት በማስፋት፣ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተደራሽነትን በማሳደግ እና የግብርና ማቀነባበሪዎችን ቁጥር በመጨመር አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግባለች። በዚህም በዜጎች ጤና እና ገቢ እድገት ላይ ለውጦች መምጣታቸውን ሪፖርቱ ያሳያል። ብሄራዊ የምግብ ስርዓት ማዕቀፎች፣ በምክክሮች የዘርፉ ተዋንያን የማሳተፍ ሁኔታ እያደገ መምጣት፣ በምግብ ስርዓቱ በሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ስር ለውጥ አምጪ ተብለው የተቀመጡ 24 መፍትሄዎች እና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ሌሎች የታዩ አበረታች ለውጦች ናቸው። ሰባቱ ስትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብን ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ፣ ጤናማ የአመጋገብ ሁኔታን መፍጠር፣ አሰራሮች እና ፖሊሲዎችን በተቀናጀ መንገድ መተግበር፣ በምግብ ስርዓቱ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እና አሰራሮችን መተግበር፣ የገበያ ተደራሽነት ማስፋት እና መረጃ አሰጣጥን ማጠናከር፣ ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን መጠበቅ እና የማይበገር አቅም መገንባት እንዲሁም መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋት፣ ዘላቂነት ያለው የከተሜነት እድገትን መፍጠር እና ክህሎት ልማት ላይ ያተኮሩ ናቸው። ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን በሚፈለገው መጠን ተደራሽ አለማድረግ፣ ደካማ የምግብ ደህንነት መሰረተ ልማት፣ የግብርና ሜካናይዜሽን አለመስፋፋት፣ የከባቢ አየር ጉዳቶች፣ የቅንጅታዊ አሰራር ላይ ያሉ ክፍቶች እና የዜጎች የአኗኗር ሁኔታ ለይ ለውጦች ቢኖሩም አመርቂ አለመሆን፣ የፋይናንስ ውስንነት እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት በምግብ ስርዓቱ ዋና ፈተናዎች ተብለው የተቀመጡ ናቸው። የምግብ ስርዓትን አስተዳደርን እና የባለድርሻ አካላት ቅንጅትን ማጠናከር፣ የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ መዋቅሮችን መዘርጋት፣ የመንግስት እና የግል አጋርነትን ማጠናከር፣ አቅምን መገንባት እና የምግብ ስርዓት አጀንዳ ዘላቂነት ባለው እና በተቀናጀ ሁኔታ ለማህበረሰቡ ማስገንዘብ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተብለው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ። የገበያ ትስስርን ማጠናከር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች እና ስትራቴጂዎችን ማቀናጀት እንዲሁም ወጣቶች፣ ሴቶች እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጨምሮ የስርዓተ ምግብ ትግበራው ሁሉን አካታችነት የበለጠ ማረጋገጥ ቀጣይ የቤት ስራ ተብለው የተያዙ ናቸው። በአጠቃላይ የስርዓተ ምግብ ማዕቀፉን በየጊዜው በመፈተሽ እና የሁኔታዎችን ተለዋዋጭነት ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ የአስተዳደር መዋቅርን በማሻሻል እ.አ.አ በ2030 የተያዙ ግቦችን ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ሁሉን አቀፍ ሪፖርቱ ያመለክታል። በአዲስ አበባ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሚካሄደው ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ በስርዓተ ምግብ ላይ እያከናወነች ያለውን ስራ ለዓለም የማሳወቅ ስራ ታከናውናለች። በስርዓተ ምግብ ትራንስፎርሜሽን ያላትን ተሞክሮዎች በዋናው ጉባኤ እና በጎንዮሽ ሁነቶች ላይ ታቀርባለች። የጉባኤው ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያን የስርዓተ ምግብ የተግባር ስራዎች እና ውጤቶች በመስክ ምልከታቸው ይቃኛሉ።
የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አሻራ ያረፈበት የኢትዮ-ታንዛንያ ወዳጅነት
Dec 17, 2024 4275
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል። የታንዛንያ የውጭ ጉዳይ እና ምሥራቅ አፍሪካ ትብብር ሚኒስትር አምባሳደር ማሕሙድ ታቢት ኮምቦ በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ትናንት አዲስ አበባ ገብተዋል። ስብስባው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ትስስር እና የጋራ ትብብር የማጠናከር ዓላማ የያዘ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም ከታንዛንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከነበሩት ጃንዋሪ ማካምባ ጋር ባደረጉት የሁለትዮሽ ውይይት የኮሚሽኑን ስብስባ ለማካሄድ ከስምምነት መድረሳቸው አይዘነጋም። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ወዳጅነት በቅርበት ለመረዳት የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄን ማየት ግድ ይላል። የመላው ጥቁር ሕዝቦች ንቅናቄ የሆነው ፓን አፍሪካኒዝም ጅማሮ በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። የፓን አፍሪካኒዝም መሰረት የሆነችው ኢትዮጵያ የንቅናቄው ፋና ወጊ በመሆን ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤ ላይ ከኢትዮጵያ ጋር አብረው በመቆም ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት አገራት መካከል ታንዛንያ ትገኝበታለች። በፓን አፍሪካኒዝም ትግል ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ መሪዎች መካከል ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ እና የታንዛንያው የቀድሞ ፕሬዝዳንት ጁሊዬስ ኔሬሬ ተጠቃሽ ናቸው። መሪዎቹ ለአፍሪካ አገራት ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ትልቅ ሚና በመጫወት ሕያው አሻራቸውን አሳርፈዋል። የኢትዮጵያና ታንዛንያ የሁለትዮሽ ግንኙነት በእነዚህ መሪዎች ጊዜ የተጀመረ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ። አገራቱ በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጣር ግንቦት 25 ቀን 1963 የቀድሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (በአሁኑ መጠሪያው የአፍሪካ ኅብረት) መቋቋሙ ሲበሰር መስራች አባል አገራት ነበሩ። ኢትዮጵያና ታንዛንያ በየአገራቱ ኤምባሲያቸውን በይፋ በመክፈት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናክር እየሰሩ ይገኛሉ። አገራቱ የሁለትዮሽ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸው በርካታ አቅሞች አሉ። ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ ባላቸው የቁም እንሥሳት ኃብት ከአፍሪካ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ አገራት ናቸው። ሁለቱ አገራት በሚያደርጓቸው የጋራ ምክክሮች ይሄን ሰፊ ኃብት በመጠቀም የንግድ እና ኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር እንደሚገባ በተደጋጋሚ ጊዜ ያነሳሉ። ግብርና፣ የሰብል ምርት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ እና አቪዬሽን ከሁለቱ አገራት የትብብር መስኮች መካከል በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ በርካታ ታንዛንያውያን ፓይለቶች እና ኢንጂነሮችን አሰልጥኖ አስመርቋል። አቪዬሽንም የሁለቱ አገራት ቁልፍ የትብብር መስክ በሚል ይነሳል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም በታንዛንያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከታንዛንያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል። አገራቱ በወቅቱ በባህልና ኪነ-ጥበብ፣ በግብርና እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል ንግድ ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቶቹ የሁለቱ አገራት ትብብር ይበልጥ ለማጠናክር ትልቅ ፋይዳ አላቸው። የዛሬው የኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባም የስምምነቶችን አፈፃጸም በመገምገም ትግበራውን ማፋጠን የሚያስችል አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከሰሞኑ የምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት አካል የሆነው ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የተዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ይታወቃል። የቀጣናው ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ (ሃይዌይ) ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ኢትዮጵያና ኬንያን ያስተሳሰረ መሆኑ ይታወሳል። የፕሮጀክቱ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ ከኬንያ ወደ ታንዛኒያ የተዘረጋ ሲሆን የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት መጀመሩን የውኃና ኢኒርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። ይህ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን እና የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው። የኃይል አቅርቦት መጀመሩ ከኢትዮጵያ እና ታንዛንያ አልፎ በቀጣናው ያለውን ትስስር ለማፋጠን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል። ሁለቱ አገራት በቅርቡ ወደ ትግብራ ምዕራፍ የገባው የናይል የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን በአገራቸው ፓርላማ ማጽደቃቸው ይታወቃል። ስምምነቱ በናይል ተፋስስ የውኃ ኃብትን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ በበጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው። አገራቱም በውኃ ኃብት ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ነው። የፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ ያስተሳሰራቸው ኢትዮጵያ እና ታንዛንያ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ትብብራቸውን ወደ ቀጣዩ ምዕራፍ ማሸጋግር የሚያስችሉ ሰፊ እድሎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።
ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረው የኢትዮ-አልጄሪያ ወዳጅነት
Dec 16, 2024 3735
የኢትዮ-አልጄሪያ ግንኙነት ታሪካዊ ነው፡፡ታሪካዊነቱ በዘመንም፣ በጸና ወዳጅነትም ይለካል።ትናንት ማምሻውን የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የሀገሪቷን ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልክዕት ይዘው አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወቃል። ዛሬ ማለዳ ደግሞ ሚኒስትሩ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ሁለቱ ሀገራት ያላቸውን የፀና ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናግረዋል። የፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔን መልዕክትም ተቀብለዋል። ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰሜን አፍሪካዊቷ አልጄሪያ እና የኢትዮጵያን ወዳጅነት የትመጣ እና ሂደት በወፍ በረር እንቃኝ። የኢትዮ-አልጀሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሰባት አስርት ዓመታትን ተሻግሯል። ሁለቱ ሀገራት ከመደበኛ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ወንድማማችነትና ወዳጅነት መስርተዋል። የፈረንሳይ ቅኝ ተገዥ የነበረችው አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ 1960ዎቹ መባቻ ነጻነቷን ለመቀዳጀት ትንቅንቅ ላይ በነበረችበት ዘመን ኢትዮጵያ አጋርነቷን አሳይታለች። ይህን ደግሞ በኢትዮጵያ የአልጄሪያ አምባሳደር የነበሩት ኤልሃምዲ ሳላህ ‘አልጀሪያ የኢትዮጵያን ውለታ አትረሳውም’ ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2022 ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀው ነበር። አልጀሪያ በ1962(በአውሮፓዊያኑ) ነበር ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻነቷን ያረጋገጠችው። ከዚህ ዘመን ጀምሮ ሁለቱ ሀገራት ወዳጅነታቸውን መሰረቱ። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና የፓን አፍሪካኒዝም እንዲያብብ ንቅናቄ አድርገዋል። በ1960ዎቹ መጨረሻም ይፋዊ ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ። አልጄሪያ የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት(የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ኤምባሲዋን በ1976(እ.ኤ.አ) ከፈተች። ኢትዮጵያም በ2016 ኤምባሲዋን በአልጀርስ ከፍታለች። ሁለቱ ሀገራት በአውሮፓዊያኑ 2014 በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ንግድ፣ ባህል እና በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል የጋራ ኮሚቴ ፈጥረዋል። ሁለቱ ሀገራት በንግድ፣ ኢንቨስትመንት ጥበቃ እና ማስተዋወቅ እንዲሁም ተደራራቢ ታክስ ማስቀረትን ጨምሮ ከ20 በላይ የትብብር መስኮች በጋራ መስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከሁለትዮሽ ባሻገርም ቀጣናዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የትብበር መስኮች ያላቸውን ትብብር የማጠናከር ፍላጎት አላቸው። ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በነበሩበት ወቅት በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 79ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ከአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መወያየታቸው ይታወቃል። በዚሁ ውይይት ኢትዮጵያ እና አልጄሪያ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን አልፎም በዓለም የሰላም እና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል። አምስተኛውን የኢትዮ-አልጄሪያ የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርብ ጊዜ ለማከናወን የተጀመረውን ዝግጅት ለማፋጠን ተስማማተዋል። አልጄሪያ የአፍሪካ ሕብረት የሰላም እና የጸጥታ ምክር ቤት ከአውሮፓዊያኑ ጃንዋሪ 2024 አንስቶ የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ተለዋጭ አባል ሆና በመስራት ላይ ትገኛለች። ይህም ሁለቱ ሀገራት በባለብዝሃ ወገን የዲፕሎማሲ መድረክ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ የሚያጎለብት ነው። አልጄሪያ በአውሮፓዊያኑ በ2021 የአረብ ሊግ ሊቀመንበር በነበረችበት ወቅት ተቋሙ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተዛባ አረዳድ ለማስተካከል እና ሚዛናዊ እይታ እንዲኖረው ጥረት አድርጋለች። የኢትዮ-አልጄሪያ የሁለትዮሽ ትብብር የሚያጠናክሩ የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እያደጉ መጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም በአልጄሪያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸው ይታወቃል። በወቅቱም ከአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብደልማጂድ ቴቡኔ ጋር ተወያይተው ነበር።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮ-አልጄሪያ ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪካዊ በሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር የሚቻለባቸው ዘርፎች እንዳሉ ገልጸው ነበር። ከዚህ ጊዜ ጀምሮም በሀገራቱ መካከል የጉብኝት ልውውጦች እና ውይይቶች እየጨመሩ መጥተዋል። ለአብነትም በአውሮፓዊያኑ በ2021 የያኔው የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ራምታኔ ላማምራ በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው ነበር፤ የሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም አይዘነጋም። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ደግሞ በሩሲያ ሶቺ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም ከተካሄደው የመጀመሪያው የአፍሪካ-ሩሲያ የትብብር ፎረም የሚኒስትሮች ስብስባ ጎን ለጎን ከአልጄሪያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጋር መክረዋል። በውይይታቸውም የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያስጠብቁ ቀጣናዊና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። እናም ሁለቱ ሀገራት በተለያዩ የትብብር መስኮች ግንኙነታቸውን ማጎልበት ቀጥለዋል። በአልጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር መሀመድ ዋሬ በቅርቡ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአልጄሪያው ፕሬዝዳንት አብዱልመጂድ ቴቡኔ ሲያቀርቡ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ልባዊ ሰላምታ እና የወዳጅነት መልዕክት ለፕሬዝዳንቱ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው። ዛሬ ደግሞ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ የሚገኙት የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ የፕሬዝዳንት አብደልመጂድ ቴቡኔን መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አድርሰዋል። የሚኒስትር አሕመድ አታፍ ጉብኝት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያለው እና የኢትዮ-አልጀሪያ ሁለትዮሽ ወዳጅነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ የሚደረገው ጥረት አካል ስለመሆኑ የአልጄሪያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ አታፍ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ጋርም ተወያይተዋል። በውይይቱ በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው። ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው አገራቱ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትስስር በማጠናከር እና አዳዲስ የትብብር አድማሶችን በመፈለግ አጋነታቸውን ለማጎልበት እንደሚሰሩ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ እና አልጄሪያ የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብስባን በቅርቡ ለማድረግ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። እናም ኢትዮጵያና አልጄሪያ ከተለምዷዊ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር የተሻገረ ነው። ሁሉን አቀፍ በሆኑ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ባደረጉ ትብብር መስኮች እየተወዳጁ ነው። የስትራቴጂካዊ አጋርነት ደረጃ እየጎለበተ ይመስላል። የአገራቱ መጻዒ የትብብር ጊዜ ብሩህ እና ፍሬያማ እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ልዩ ዘገባዎች
ባጃጅ ላይ ወድቆ የተገኘው የአደራ ገንዘብ- 82 ሺህ 265 ብር
Mar 5, 2025 3969
በአማራ ክልል ዋግኸምራ አስተዳደር የሰቆጣ ከተማ ነዋሪው ባለባጃጅ ወጣት ሠለሞን ቢምረው ተሳፋሪ ደንበኞቹን ከቦታ ቦታ በማዘዋወር ዕለታዊ ተግባሩን ይከውናል። ዛሬ ማለዳ ታዲያ በሰቆጣ ወረዳ የሰርክ ተግባሩን እያከናወነ ሳለ በድንገት ከአንድ ተሳፋሪ የተረሳ በኬሻ የተቀመጠ ንብረት ባጃጁ ውስጥ ያገኛል። ሰለሞን ቢምረው ማንነቱን ባላወቀው ተሳፋሪ የተረሳው ምንነቱን ያላወቀው በኬሻ የተቋጠረ ንብረት ገንዘብ መሆኑን ያወቀው ከደቂቃዎች በኋላ ነበር። 'ታማኝነት ለራስ ነው' የሚለው ወጣት ሰለሞን፥ ከተሳፋሪ ደንበኛ የተረሳን መጠኑን ያላወቀው ገንዘብ ለመመለስ ተጣደፈ። ተሳፋሪውን በእግር በፈረስ ማፈላለግ ይጀምራል። በሌላ በኩል የሰቆጣ ወረዳ ነዋሪዋ ወይዘር ኃይሌ በአደራ የተረከቡትን በኬሻ የተቋጠረ 82 ሺህ ብር በላይ ገንዘብ ፌርማታ ላይ ከባጃጅ ሲወርዱ መርሳታቸውን ካወቁበት ቅጽበት ጀምሮ በደንጋጤ ድባቴ ውስጥ ገብተዋል። ጉዳያቸውን ለፖሊስ አሳውቀው የአደራ ገንዘባቸውን በይገኛል ተስፋ እና ጭንቀት የባጃጅ አሽከርካሪውን ፍላጋ በየፌርማታው እየኳተኑ ነው። ተሳፋሪ እና አሳ'ፋሪ በየፊናው መፈላለጉን ተያያዙት። በዚህ መሀል የባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን ቢምረው ወደ ተሳፋሪዋ ወይዘር ኃይሌ ድንገት ከተፍ ይላል። የወይዘሮ ወይዘር ደስታ ወደር አጣ። አሳፋሪው ሰለሞንም እፎይታ ተሰማው። በተለይ የአደራ ገንዘብ መሆኑን ሲረዳ። ባጃጅ አሽከርክሪው ሰለሞን እና ተሳፋሪዋ ወይዘሮ ወይዘር በፖሊስ ፊት ንብረት ተረካከቡ። ወጣቱ ሰለሞን እንደገለጸው የተሳፋሪ ንብረት በመመለሱ ደስተኛ ነው። ለወይዘሮ ወይዘር አደራ ያስረከበችው የገንዘቡ ባለቤት ወይዘሪት ወለለ ንጉስ፤ በሰለሞን ቢምረው ነባይነት(ታማኝነት) እንዳስገረማቸው ይናገራሉ። በዚህ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አግኝቶ መመለስ በዕውነቱ በነፍስም በስጋም የሚያስመሰገን በጎ ምግባር ነው ስትል አመስግናለች። የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ደሳለኝ አባተ ወጣት ሰለሞን ከአሁን ቀደምም ሞባይል ጥለው የሄዱትን ለባለቤቱ በታማኝነት መመለሱን አስታውሰዋል። አሁን ደግሞ በኬሻ የተቋጠረን 82 ሽህ 265 ብር ከግል ይልቅ የህዝብን ጥቅም በማስቀደም ለግለሰቧ በታማኝነት ማስረከቡን አረጋግጠዋል። ይህን መሰል በጎ ምግባር በሁሉም የማህበረሰብ ዘንድ በአርዓያነት ሊወሰድ የሚገባው ነው ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
"የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ"- የዕልፍ ሕጻናት አድኑ ላሌ ላቡኮ አዲስ ፍኖት
Dec 13, 2024 3145
ሚንጊ የታዳጊዎችን ተስፋና ሕልም ብቻ ሳይሆን ሕልውና የነጠቀ ጎጂ ባህላዊ ልማዳዊ ድርጊት ነው። በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን እንደ ካራ፣ ሀመርና ቤና ህዝቦች ዘንድ የሚዘወተረው ሚንጊ፤ በአካባቢው ልማድ በታችኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ቅዱስ፣ በላይኛው ድድ ጥርስ የሚያበቅሉ እንስሳት ደግሞ ርኩስ የሚል ስያሜ ይሰጣል። የላይኛው የወተት ጥርሳቸው ቀድሞ የሚበቅል ሕጻናት እንደ እርኩሳን እንስሳት ከመጥፎ መንፈስ ጋር ተቆጥሮ ለማህበረሰቡ የማይበጅ፣ አድጎም ለቤተሰቡ ጠንቅ ተቆጥሮ የመገደል ዕጣ ፈንታ ይገጥማቸዋል። በተመሳሳይ በማህበረሰቡ አባል ሴት ከትዳር በፊት ልጅ ከወለደች የተወለደው ሕጻን በ'ሚንጊ'ነት ይፈረጃል። በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናት ደግሞ መርገምት፣ ቁጣ፣ ርሀብ በሽታ… መንስዔ እንደሚሆኑ ታምኖ ከጥልቅ ወንዝ መጣል፣ ወደ ገደል መወርወር አልያም በጫካ ውስጥ የመጣል መጥፎ ዕጣ ይጠብቃቸዋል። ቤተሰባቸውን በዚህ ጎጂ ባህላዊ ድርጊት ያጡት አቶ ላሌ ላቡኮ 'ሚንጊ'ን ከመሰረቱ ለመንቀል 'የኦሞ ቻይልድ' መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በማቋቋም ውጤታማ ስራዎች አከናውነዋል። አሁን ደግሞ የእስካሁን ጥረቶችን ተቋማዊ መልክ በመስጠት 'ሚንጊ'ን በዘላቂነት ማስቀረት የሚያስችል ተቋም አስመርቀዋል። ይህም በደቡብ ኦሞ ዞን ካራ-ዱስ ቀበሌ በዛሬው ዕለት የተመረቀው "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ነው። አካዳሚውን በምክትል ርዕሰ መሰተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። ዕልፍ ህፃናትን ሕይወት የቀጠፈና ወላጆችን የወላድ መካን ያደረገውን የሚንጊ "ልብ ሰባሪ" ድርጊት ለማስቀረት እንደ ላሌ ላቡኮ ባሉ ቅን ልቦች ብርቱ ተጋድሎ መልከ ብዙ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ቢሮ ኅላፊው ገልጸዋል። ያም ሆኑ ይህን ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በዘላቂነት ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እንደሚጠይቅ ይናገራሉ። በዕለቱ የተመረቀው አካዳሚም የክልሉ መንግስት በአርብቶ አደሩ አካባቢ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ከባህል ተፅዕኖ ተላቀው መማር እንዲችሉ የሚያግዝ እንደሆነ አብራርተዋል። በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ደግሞ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ ይገልጻሉ። ሚንጊን ለማስቀረት ከማህበረሰቡ የባህል መሪዎች ጋር በመቀናጀት በተከናወኑ ስራዎች የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ መሆኑን ያነሳሉ። እናም ወትሮ በ'ሚንጊ'ነት የሚፈረጁ ሕጻናት ዛሬ ላይ "የአብራካችን ክፋይ፤ የኛ ልጆች" ተብለው በወላጆች ዕቅፍ ማደግ መጀመራቸውን ይገልጻሉ። የኦሞ ቻይለድ መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ላሌ ላቡኮ፤ "ይህን መሰል ጎጂ ልማድ ድርጊት ማስወገድ በቀላሉ የሚታሰብ ሳይሆን እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ዋጋ መክፈል ይጠይቃል" ይላሉ። ያም ሆኖ ራሳቸውን ለመስዕዋትነት ዝግጁ በማድረግ ድርጊቱ እንዲቀር ማድረግ ስለመቻላቸው ያነሳሉ። በእርሳቸው ድርጅት ብቻ ላለፉት 15 ዓመታት ከ60 በላይ በ'ሚንጊ'ነት የተፈረጁ ሕጻናትን ሕይወት እና ሕልም በመታደግ ለሀገር ኩራት እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል። "ትምህርት ባይኖር በልበ ሙሉነት ማውራት አልችልም ነበር" የሚሉት አቶ ላሌ፤ "የኦሞ ቻይልድ የወደፊት መሪዎች አካዳሚ'' ባለብሩህ አዕምሮ ሀገር ተረካቢ ሕፃናት የሚፈልቁበት ማዕከል እንደሚሆን አረጋግጠዋል።
የአርሶ አደሮችን ጓሮና ኑሮ የለወጡ ቁጥሮች- “30-40-30”
Nov 15, 2024 4662
ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ የሚሆን ሃብት የሰነቀው የ"30-40-30" ኢኒሼቲቭ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሮች መንደር ተገኝቶ ስለ ’30-40-30’ አሃዞች አርሶ አደሮችን የሚጠይቅ ካለ የቁጥሮችን ትርጓሜና ስሌት በቅጡ መረዳት ይችላል። እነዚህ ቁጥሮች በገጠራማው የክልሉ አካባቢዎች አባውራዎች ዘንድ ሕይወትም፣ አስተሳስብም ለውጠዋልና። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኅላፊ አቶ ዑስማን ሱሩር የ’30-40-30’ ኢኒሼቲቭ የተጠነሰሰው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭን በመመርኮዝ ስለመሆኑ ያስታውሳሉ። እነዚህ ቁጥሮች የተራ አሃዝ ስያሜ ሳይሆኑ በክልሉ ግብርና ወደ እመርታ ለማስፈንጠር የተቀየሱና ትውልድ ተሻጋሪ ዓላማ የሰነቁ ናቸው። በ2014 ዓ.ም ጀምሮ እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 100 የፍራፍሬ ዛፎች አልምቶ እንዲጠቀም መሰረት የሆኑም ናቸው። በኢኒሼቲቩ የለሙ ፍራፍሬዎች የአርሶ አደሩን ኑሮ ማሻሻል ያለሙ፣ 'ለዛሬው ትውልድ ምግብ፣ ለመጪው ትውልድ ደግሞ ቅርስና ውርስ ናቸው' ይላሉ። የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ገቢ ምንጭ ማድረግ፣ ስራ ዕድል መፍጠር፣ ገበያ ማረጋጋት፣ ለኤክስፖርትና ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማቅረብን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዓላማዎችም አሏቸው። በእያንዳንዱ አባውራ ጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲለማና ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል የተወጠነ ነው። በዚህም በ'30-40-30'ን እያንዳንዱ አባወራ ጓሮውን እንደየአካባቢው ስነ-ምህዳር በሙዝ፣ በፓፓያ፣ በማንጎ፣ በቡና፣ በአቮካዶና በሌሎች ፍራፍሬ ችግኞች እንዲያለማ ተደርጓል። 'ያልተሄደበትን መንገድ በመሄዳችን በትግበራ ሂደቱ ፈተናዎች ነበሩ' የሚሉት ሃላፊው፤ ዛሬ ላይ ግን የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ ፍሬ የቀመሱትን ሁሉ አስተሳስብ ለውጧል ይላሉ። ኢኒሼቲቩ ባልተለመዱ አካባቢዎች የፍራፍሬ መንደሮች የተፈጠሩበት፣ የአርሶ አደሩ ኑሮና ጓሮ የተለወጠበት፣ የይቻላል አስተሳስብ የተፈጠረበት እንደሆነ ይናገራሉ። በክልሉ የ30-40-30 ኢኒሼቲቭ በመተግበር ከሴፍቲኔት የተላቀቁና ኑሯቸውን ያሻሻሉ አረሶ አደሮች ለዚህ ምስክር ናቸው። በስልጤ ዞን ውልባረግ ወረዳ ቶዴ ጠመዳ ነዋሪዎች አቶ ሀምዛ አሊዬ እና ባለቤታቸው አናጃ ኢሳ በሴፍትኔት ታቅፈው ሲረዱ የቆዩ ሲሆን በ30-40-30 ጓሯቸውን በቡና በማልማታቸው ዛሬ ገቢም፣ ምግብም ችለዋል። በ500 የቡና ችግኝ ድጋፍ ጀምረው በየዓመቱ እያሳደጉ ዛሬ ላይ ቡናቸውን ለቅመው በመሸጥ ገቢ ማመንጨትና ነሯቸውን መደጎም ችለዋል። ጓሯቸውን በማልማታቸውም ከሴፍትኔት መላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያላቸው ማህበራዊ ህይወት እንዲሻሻል ስለማድረጉም ገልጽው፤ በቀጣይነትም ሌሎች ፍራፍሬዎችን ለማልማት ተዘጋጅተዋል። በውልባረግ ወረዳ ቢላዋንጃ ባቢሶ ቀበሌ ነዋሪው አቶ ኢክማላ መሀመድ እና ልጃቸው መካ ኢክማላ ደግሞ አካባቢውን ያልተለመደ የሙዝ መንደር በማድረግ ኑሯቸውን እንዳሻሻሉ ይናገራሉ። የ30-40-30 ንቅናቄ ሲጀመር በአካባቢው "ሙዝ አይለማም" በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቅር እያላቸው ችግኞችን ወስደው የተከሉ ቢኖሩም በርካቶች በእምቢታ ጸንተው እንደነበር አስታውሰዋል። በሂደት ውጤቱ ሲታይ ግን የልማቱ ተሳታፊዎች በዝተው በውጤትና የስኬት መንገድ ላይ መቀጠላቸውን ተናግረዋል። ከሳዑዲ አረቢያ የ10 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ የተመለሰው ልጃቸው መካ ኢክማላ የስደት አስከፊነትን በማንሳት ተፈጥሮ በሰጠችን ጸጋ ሳንጠቀም በመቆየታችን ይቆጨናለ ይላል። የ30-40-30 ንቅናቄም ወጣቶች ከስደት ይልቅ በጓሯቸው ሰርተው መለወጥ እንደሚችሉ ዐይን የገለጠ እና የአስተሳሰብ ለውጥም ያመጣ ስለመሆኑ ይናገራል። በሀድያ ዞን ሻሸጎ ወረዳ ዶዕሻ ጎላ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ይቴቦ ሽጉጤ፤ ኢኒሼቲቩን በመጠቀም ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር የሙዝ መንደር መስርተዋል። የክላስተር ሙዝ መንደራቸው በሶስት ዓመታት ውስጥ የቤተሰባቸው ኑሮ እንዲሻሻል ያደረገና በቀላሉ ጸጋን ተጠቅሞ መለወጥ እንደሚቻል ያረጋገጠ ስለመሆኑም ገልጸዋል። የስልጤ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሙበራ ከማል፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት በሚል ንቅናቄ በርካቶች በተለይም በፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ተሳትፈው ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል። በአካባቢ ያሉ ጸጋዎችን በመለየት የቡና፣ የሙዝና የአቮካዶ ክላስተር በማልማት ከፍጆታ አልፈው ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረቡ ስለመሆኑም ይናገራሉ። በሀድያ ዞን የሻሸጎ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዶክተር ወንዱ መለሰ፤ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል። በሙዝ ክላስተር አርሶ አደሮች በትብብር ሰርተው እንዲለወጡ ያስቻለ መሆኑን ገልጸው፤ አርሶ አደሮችም ውጤቱን በማየት ወደተጨማሪ ልማት እየገቡ ይገኛሉ ብለዋል። የ30-40-30 ኢኒሼቲቩ 'ጥረት ካለ ስኬት እንዳለ ማሳየት የተቻለበት እና የግብርናው ዘርፍ አንኳር መሰሶዎችን ዕውን ለማድረግ ተስፋ ሰጭ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አቶ ዑስማን ይገልጻሉ። በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የግብዓት ፍላጎት በመጨመሩ ተደራሽነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛልም ብለዋል። የ30 40 30 የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት አንድ አርሶ ወይም አርብቶ አደር በመጀመሪያ ዓመት 30፣ በሁለተኛው ዓመት 40 እና በሶስተኛ ዓመት 30 የፍራፍሬ ችግኞችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆንበት መርሃ ግብር መሆኑ ይታወቃል።
መጣጥፍ
የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል አብዮት
Aug 27, 2025 194
በሙሴ መለስ/ኢዜአ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የአረንጓዴ ኃይል ዋንኛ ማዕከል በመሆን ላይ ትገኛለች። የተፈጥሮ ውበቷን ከኢኖቬሽን ጋር በማስተሳሰር የአየር ንብረትን የማይበክሉ የተለያዩ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን እየተጠቀመች ይገኛል። አዲስ አበባ ሁለተኛውን የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ለማስተናገድ ዝግጅቷን አጠናቃ እንግዶቿን እየተጠባበቀች ነው። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ስራ በጉባኤው ከምታቀርባቸው ተሞክሮዎች መካከል ይጠቀሳል። ኢትዮጵያ ከውሃ፣ ከፀሐይ፣ ከነፋስ፣ ከእንፋሎት ሃይል፣ ባዮማስ ከእንስሳትና እጽዋቶች ተረፈ-ምርት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም አላት። ይህም የሚያሳየው አብዛኛውን የኤሌክትሪክ ኃይል የምታገኘው ከታዳሽ የኃይል ምንጮች መሆኑን ነው። ኢትዮጵያ ከጂኦተርማል 10 ሺህ ሜጋ ዋት ከንፋስ ኃይል ደግሞ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል የማመንጨት እምቅ አቅም አላት። ግንባታው የተጠናቀቀው እና 5 ሺህ 200 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ከብክለት ነጻ የኃይል ምንጭ ከመሆን ባለፈ ለሀገሪቷ ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። መንግስት የሀገሪቱን የኃይል እጥረት ለመቅረፍ በዋና ዋናዎቹ የወንዞች ተፋሰሶች የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶችን በማልማት ላይ ይገኛል። በ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅዷ ኢትዮጵያ የምታመነጨውን የኃይል መጠን አሁን ካለበት 4 ሺህ 818 ሜጋ ዋት ወደ 17 ሺህ ሜጋ ዋት ለማሳደግ ግብ ተቀምጧል። የተሻሻለው የኢነርጂ ፖሊሲዋም ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ነባራዊ ዕውነታ መሰረት ያደረገ እና ጎረቤት ሀገራትን በኃይል መሰረተ ልማት ለማስተሳሰር ያለመ ነው። ይህንንም እውን ለማድረግ በመንግስት ከሚለሙት የኃይል ምንጮች በተጨማሪ በግሉ ዘርፍ ኃይል ተመርቶ የኃይል አቅርቦቱ እንዲሻሻልና ዘላቂ እንዲሆን አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ ይህንንም እውን ለማድረግ በ2009 ዓ.ም በገንዘብ ሚኒስቴር ስር የመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ፕሮጀክት በአዋጅ ቁጥር 1076/2018 ተመስርቷል። በዚህ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ስምንት የፀሐይ ኃይል፣ አምስት የሃይድሮ ኤሌክትሪክ እና አምስት የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶችን ለማልማት እየተሰራ ይገኛል። ከስምንቱ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እስከ 750 ሜጋ ዋት ኃይል ለማግኘት መታቀዱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መረጃ ያመለክታል። ጋድ 1 እና 2፣ ዲቼቶ፣ ወራንሶ፣ ሁመራ፣ ወለንጪቲ፣ መቀሌ፣ ሁርሶ እና መተማ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶቹ ናቸው። አዳማ አንድ፣ አዳማ ሁለት፣ አይሻ ሁለት እና አሸጎዳ ከንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶቹ መካከል ይጠቀሳሉ። የእንፋሎት (ጂኦተርማል) ኃይልን በተመለከተም በመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ፕሮጀክት ኮርቤቲ ከሚባል የግል አልሚ ጋር መንግስት ተዋውሎ ድርጅቱ የሚያመርተውን 150 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢትዮጵያ ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል። በአጠቃላይ በተለያዩ የኢነርጂ አማራጮች የኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት ሽፋንን 54 በመቶ ማድረስ መቻሉን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። በብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም አማካኝነት እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2030 65 በመቶ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከብሔራዊ የኃይል ቋት እንዲሁም ቀሪው 35 በመቶ ከኃይል ቋት ውጭ ባሉ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ የማድረግ እቅድ ተይዟል። ኢትዮጵያ ከራሷ አልፋ ለምስራቅ አፍሪካ ሀገራት እያቀረበች ያለው አረንጓዴ የኃይል አማራጭ የአየር ንብረት ተጽእኖን ለመከላከል እና ከባቢ አየርን ለመጠበቅ ያላትን ጠንካራ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው። የተሻሻለው የኢነርጂ ፖሊሲዋም ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ነባራዊ ዕውነታ መሰረት ያደረገ እና ጎረቤት ሀገራትን በኃይል መሰረተ ልማት ለማስተሳሰር ያለመ ነው። በርግጥ ከሕዳሴው ግድብ ባሻገር ሌላው ከአፍሪካ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የኮይሻ ኃይል ማመንጫም ለቀጣናዊ ትስስር መፋጠን ሌላው እድል ነው። በጥቅሉ ኢትዮጵያ ለጎረቤት አገራት የምታቀርበው የኤሌክትሪክ ኃይል የሀገራት ኢኮኖሚ ትብብር የሚያጠናክር እና የኢትዮጵያን የመሰረተ ልማት የማስተሳሰር ጽኑ ፍላጎት ማሳያ ነው። በተጨማሪም በቀጣናው ዘላቂ የኤሌክትሪክ ገበያ ልማትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ክፍለ አሕጉራዊ ጥረት ነው። ጥረቱ የምሥራቅ አፍሪካ የሃይል ቋት (The Eastern Africa Power Pool-EAPP) በቀጣናው ሀገራት መካከል ድንበር ተሻጋሪ የሃይል ንግድ እና የሃይል መስመር ትስስርን ለማሳለጥ እኤአ በ2005 የተቋቋመ ተቋም ግብ እውን ከማድረግ ባለፈ አሕጉራዊ ምጣኔ ሃብታዊ ትስስርን ያፋጥናል። የኢትዮጵያ የታዳሽ ኢነርጂ አብዮት የአየር ንብረት ለውጥ የመከላከል ስራ እና የደን ልማትን የሚያግዝ ነው። ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ እየተቃረበ ባለበት ወቅት ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኃይል አሻራውን ለአፍሪካ ለማሳየት ተዘጋጅታለች። አረንጓዴ የኃይል አማራጮች ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት የማይበገር ኢኮኖሚ መገንቢያ ዋና ምሰሶዎች መካከል ይጠቀሳል።
የኢትዮጵያ የካርቦን ገበያ፤ፍትሃዊ የአየር ንብረት ፋይናንስ አቅርቦት ማግኛ አማራጭ ---
Aug 26, 2025 277
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፤ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" የጉባኤው መሪ ሀሳብ ነው። ከጉባኤው አጀንዳዎች መካከል የአፍሪካ የካርቦን ሽያጭ ይገኝበታል። የካርቦን ንግድ ማለት የካርቦን ዳይኦክሳይድ እና ሌሎች የአየር ንብረት ለውጥን የሚያስከትሉ ጋዞችን ልቀትን ለመቆጣጠር የሚደረግ የገበያ ዘዴ ነው። ልክ እንደ ሌሎች ምርቶች ሁሉ የካርቦን ልቀትን የመገበያያ ዕቃ አድርጎ ይቆጥረዋል። መንግስታት ወይም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ኩባንያዎች ወይም ተቋማት ሊለቁት የሚችሉትን ከፍተኛውን የካርቦን መጠን ይወስናሉ።ይህ መጠን “የልቀት ጣሪያ” (Emission Cap) ይባላል። ከዚያም እያንዳንዱ ኩባንያ ይህን ያህል ካርቦን የመልቀቅ “ፈቃድ” ወይም “ክሬዲት” (Credit) ይሰጠዋል። ካርቦን ክሬዲት፦ ኩባንያዎች እንደ ደን ልማት ወይም የታዳሽ ኃይልን በመሳሰሉ ፕሮጀክቶች ላይ ኢንቨስት በማድረግ ብድር የሚያገኙበት ስርአት ነው። የካርቦን ንግድ ሀገራት፣ኩባንያዎች እና ግለሰቦች በተገዢነት እና በፈቃደኝነት ላይ ተመስርተው የሚያከናወኑት ነው። አፍሪካ በዓለም ደረጃ ወደ ከባቢ አየር በሚለቀቀው በካይ ጋዝ ልህቀት ከአራት በመቶ ያነሰ ድርሻ ቢኖራትም የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ዳፋ ተሸካሚ አህጉር ሆናለች። የካርቦን ገበያ ለአፍሪካ ሀገራት የአየር ንብረት ፋይናንስ እንዲያገኙ ከማድረግ ባለፈ ለስራ እድል እና ለብሄራዊ አየር ንብረት ለውጥ ማጣጣሚያ እቅዶች ትግበራ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የአፍሪካ ሀገራት በ2015 ዓ.ም በግብጽ ሻርም አል ሼክ በተካሄደው 27ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንበረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ-27) የአፍሪካ ካርቦን ገበያ ኢኒሼቲቭ ይፋ አድርገዋል። በኢኒሼቲቩ አማካኝነት አፍሪካ በዓመቱ በ300 ሚሊዮን የካርቦን ክሬዲት ስድስት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዳለች። እ.አ.አ በ2030 በካርቦን ንግድ ለ30 ሚሊዮን ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር ውጥን ተይዟል። የካርቦን ገበያ በአፍሪካ ሀገራት ተስፋ ሰጪ እድገት እያሳየ ይገኛል። ኢትዮጵያን ጨምሮ ኬንያ፣ ጋና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሩዋንዳ እና ሴኔጋል የካርቦን ገበያ የአሰራር ማዕቀፎችና ግቦች አዘጋጅተው እየሰሩ ይገኛል። የአፍሪካ ልማት ባንክም የካርቦን ገበያ የፋይናንስ አማራጭ በማዘጋጀት ሀገራት ማዕቀፎች እንዲቀርጹና የካርቦን ክሬዲት በአፍሪካ የአክሲዮን ገበያዎች ውስጥ እንዲካተቱ አድርጓል። የአፍሪካ ሕብረት የልማት ኤጀንሲ (አውዳ-ኔፓድ) በአህጉሪቷ የካርቦን ገበያ ቀረጻ፣ ትግበራ እና የግብይት ስርዓቱን የሚወስን “African Gold Standard” የተሰኘ የአሰራር ማዕቀፍ አዘጋጅቶ እየተገበረ ይገኛል። ማዕቀፉ የካርቦን ገበያ ማህበረሰቦች ካርቦንን በማመቅ ስራቸው ተጨባጭ ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥና ለብዝበዛ እንዳይጋለጡ ክትትልና ድጋፍ የሚደረግበት መንገድ ነው። የአየር ንብረት ጉባኤውን የምታዘጋጀው ኢትዮጵያ በካርበን ገበያ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ እየሰራች ትገኛለች። ኢትዮጵያ ሙቀት አማቂ ጋዞች ልቀት ቅነሳና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት የ10 ዓመት መሪ የልማት እቅድ ቀርጻ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ እንደሆነች የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። የእርምጃዎቹ አንድ አካል የሆነው የካርቦን ግብይትን በውጤታማነት ለመምራትና ተጠቃሚ ለመሆን ብሔራዊ የካርበን ግብይት ስትራቴጂ አዘጋጅታለች። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የካርቦን ግብይት ስትራቴጂ የመጨረሻ ረቂቅ ግምገማ እና የካርቦን ገበያ የህግ ማዕቀፍ የህግ ክፍተት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት (Validation Worksop on draft Ethiopia’s National Carbon Market Strategy and Consultation on the Legal Gap Analysis Report) ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በግንቦት ወር 2017 ዓ.ም በቢሾፍቱ አካሄዶ ነበር። የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን ስትራቴጂውን በፍጥነት ወደ ስራ ለማስገባት ከስትራቴጂ ዝግጅቱ ጎን ለጎን የካርቦን ገበያ ሊመራበት የሚችል የህግ ማእቀፍ ለማዘጋጀት የህግ ክፍተት የዳሰሳ ጥናት መካሄዱን ገልጸዋል። የማዕቀፉ ዓላማ በኢትዮጵያ በአግባቡ ተግባራዊ ሊደረግ የሚችል የህግ ማዕቀፉን በፍጥነት አዘጋጅቶ በማጸደቅ የካርቦን ግብይት ላይ በንቃት እና የኢትዮጵያን ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ መሳተፍ እንደሆነ ተናግረዋል። በመድረኩ ላይ የካርቦን ገበያ ልማት ስትራቴጂ ረቂቅ ሰነድ እና የካርቦን ገበያ ንግድ የህግ ማዕቀፍ ዳሰሳ ጥናት ሰነድ ግብአቶችን አካቶ በማዳበር ያሉትን ሂደቶች በማለፍ በቅርብ ጊዜ ወደ ስራ እንዲገባ አቅጣጫ ተሰጥቷል። ብሔራዊ የካርቦን ገበያ ሽያጭ ስትራቴጂ መዘጋጀቱ ኢትዮጵያ በደን ልማት፣በትራንስፖርት፣ በቆሻሻ አወጋገድና በኃይል አማራጭ ልማት ላይ በምታበረክተው ልክ ተጠቃሚ የሚያደርጋት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። በዚህም ሙቀት አማቂ ጋዞችን በመቀነስ፣ አረንጓዴ ኢኮኖሚ በማሳለጥና የዜጎችን ተጠቃሚነት በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ስራን ለማገዝ ጉልህ ፋይዳ ያለው መሆኑን አመልክቷል። ኢትዮጵያ ከኖርዌይ በየካቲት ወር 2016 ዓ.ም የተፈራረመችው የ75 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የካርቦን ሽያጭ ስምምነት በካርቦን ግብይቱ እያገኘች ያለውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያሳይ ነው። እ.አ.አ እስከ 2026 ድረስ የሚቆየው ስምምነት ከካርበን ሽያጭ የሚገኘውን ገቢ እንደ ሀገር የተሰሩ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ለማጠናከር እንዲሁም አዳዲስ የደን ልማት ስራዎችን ለመስራት ይውላል። በባሌና ምዕራብ አርሲ ጥብቅ ደኖች ሲተገበር በቆየው የበካይ ጋዞች ቅነሳና የደን ጭፍጨፋን የመቀነስ ፕሮጀክት (ሬድ ፕላስ) አማካኝነት እየተከናወነ ያለው የካርቦን ንግድ በሚሊዮኖች ብር የሚቆጠር ብር ገቢ እየተገኘበት ነው። ፕሮጀክቱ በመተግበሩ ጉዳት ይደርስበት የነበረው የደን ሀብት መጠበቅ እና የካርቦን ጋዝ ልቀትን ማስቀረት ተችሏል። ኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራን ጨምሮ የካርቦን ገበያ ተጠቃሚነቷን ለማሳደግ በሀገሪቷ የተለያዩ ጥብቅ ደኖች ካርቦኖችን በማከማቸት ገቢ እንዲገኝ እየሰራች ነው። የካርቦን ግብይት የኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ፋይናንስ የማግኘት አማራጭ በማስፋት ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ በመገንባት እና የካርቦን ገበያ የአሰራር ማዕቀፍ በመዘርጋት እያከናወነች ያለው ስራ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ምሳሌ የሚሆን ነው። በሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤም በካርቦን ገበያ ያላትን ተሞክሮ ታቃርባለች ተብሎ ይጠበቃል። በጉባኤው ላይ የካርቦን ገበያ የበካይ ሀገራት እና ኩባንያዎች የገንዘብ መክፈያ ዘዴነት ወጥቶ በአፍሪካውያን ባለቤትነት እንዲመራ መሪዎች ጠንካራ ጥሪ እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል። አፍሪካ በጉባኤው ላይ ጠንካራ የካርቦን ገበያ አስተዳደር ስርዓት መገንባት፣የካርቦን ክሬዲት ሽያጭ ላይ የሚያጋጥሙ የክፍያ ክፍተቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ ማድረግ፣ የማህበረሰብ ተጠቃሚነትን የበለጠ ማረጋገጥ፣ ተጠያቂነትን ማስፈን እና ፍትሃዊ ገቢ ማግኘት ላይ ለውጥ የሚያመጡ ውሳኔዎችን ማሳለፍ እንዳለባቸው የዘርፉ ባለሙያዎች ይመክራሉ። የካርቦን ገበያ በተገቢው ሁኔታ የሚፈጸም እና የአፍሪካን ባለቤትነት የሚያረጋግጥ ከሆነ ለአህጉሪቷ ዘላቂ የፋይናንስ አማራጭ፣ አይበገሬነትን ለመገንባት እና ዘላቂ እድገትን ለማምጣት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።