የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል - ኢዜአ አማርኛ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 26ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 11/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት መርሃ ግብር የመጀመሪያ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
ወላይታ ድቻ ከሀድያ ሆሳዕና ከቀኑ 9 ሰዓት፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
መርሃ ግብሩ ነገም ቀጥሎ ሲውል ኢትዮጵያ ቡና ከሲዳማ ቡና እንዲሁም አርባምንጭ ከተማ ከስሑል ሽሬ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የ26ኛ ሳምንት መርሃ ግብር እስከ ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።
ኢትዮጵያ መድን ሊጉን በ48 ነጥብ እየመራ ሲሆን ኢትዮጵያ ቡና በ39 ነጥብ ይከተላል።
ባህር ዳር ከተማ እና ወላይታ ድቻ በተመሳሳይ 37 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው ሶስተኛ እና አራተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ሃዋሳ ከተማ፣ አዳማ ከተማ፣ ስሑል ሽሬ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ15ኛ እስከ 18ኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛሉ።
የአርባምንጭ ከተማው አህመድ ሁሴን እና የሃዋሳ ከተማው ዓሊ ሱሌይማን በተመሳሳይ 10 ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን እየመሩ ነው።
የኢትዮጵያ ቡናው አንተነህ ተፈራ እና የፋሲል ከነማው ጌታነህ ከበደ በተመሳሳይ 9 ጎሎችን በማስቆጠር ይከተላሉ።