ሀድያ ሆሳዕና ከድል ጋር ታርቋል - ኢዜአ አማርኛ
ሀድያ ሆሳዕና ከድል ጋር ታርቋል
አዲስ አበባ ፤ሚያዚያ 11/2017 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት የመጀመሪያ መርሃ ግብር ሀድያ ሆሳዕና ወላይታ ድቻን 3 ለ 1 አሸንፏል።
በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ብሩክ በየነ፣ በየነ ባንጃ እና ደስታ ዋሚሾ የማሸነፊያ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።
ዘላለም መንግስቱ ለወላይታ ድቻ ብቸኛዋን ግብ አስቆጥሯል።
ውጤቱን ተከትሎ ሀድያ ሆሳዕና በሊጉ ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ አሸናፊነት ተመልሷል። ቡድኑ በ37 ነጥብ ደረጃውን ከ8ኛ ወደ 4ኛ ከፍ አድርጓል።
በውድድር ዓመቱ 10ኛ ድሉን አግኝቷል።
በአንጻሩ በሊጉ 7ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ወላይታ ድቻ በ37 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበልጦ 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ምሽት 12 ሰዓት ላይ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ይጫወታሉ።