አየር መንገዱ ወደ ናይጄሪያ ኢኑጉ ከተማ የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት አቋረጠ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2017(ኢዜአ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ናይጄሪያዋ ኢኑጉ አካኑ ኢብያም ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሚያደርገውን በረራ እስከ ሚያዝያ 28 ቀን 2017 . ድረስ ማቋረጡን አስታወቋል።

በረራው የተቋረጠው በአውሮፕላን ማረፊያው እየተከናወነ በሚገኘው የጥገና ሥራ ምክንያት መሆኑንም አየር መንገዱ ገልጿል።

በበረራው መቋረጥ ምክንያት ደንበኞቹ ላይ ለሚደርሰው መጉላላት ይቅርታ የጠየቀው አየር መንገዱ፣ ውሳኔው የደንበኞቹን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል የተደረገ መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

ደንበኞች ለሚኖራቸው ማንኛውም ጥያቄ የሚከተሉትን አድራሻዎች መጠቀም እንደሚችሉም ገልጿል።

Ethiopian Airlines Global Customer Interaction Center at +251 116 179 900

Ethiopian Airlines Enugu Office at +2347033745716, +2349033265850

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም