የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) በብፁዕ ወቅዱስ ፍራንሲስ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2017(ኢዜአ):- የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በብፁዕ ወቅዱስ ፍራንሲስ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

ዋና ፀሐፊው በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት የሀዘን መግለጫ መልዕክት የካቶሊክ እና የዓለም ክርስቲያን ማህበረሰብ ትልቅ የሃይማኖት አባት አጥተዋል ሲሉ ገልጸዋል።

ሊቀ ጳጳሱ ለአምላክ፣ ለቤተ ክርስቲያኗ እና ለሰብዓዊነት በተሰጠ አገልግሎታቸው ሁሌም ሲታወሱ ይኖራሉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም